የቤንች ሸኮ ዞን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ከሚገኙ 6 ዞኖች አንዱ ነዉ፡፡ከሀገራችን ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ በ585 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ዞኑ በ6 ወረዳዎችና 2 ከተማ አስተዳደሮች የተዋቀረ የአስተዳደር እርከን ያለው ሲሆን ጠቅላላ የቆዳ ስፋቱ 4,668 ካሬ ሜትር ስኩዌር እና ከባህር ወለል በላይ ከ501 እስከ 2500 ሜትር ያላቸዉ አካባቢዎች በዉስጡ ይይዛል፡፡
በ2013 በተገኘው ትንበያ መሰረት ዞኑ ከ15.1 – 22.5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ሙቀት የሚያገኝ ዞን ነው።
በ1999 ዓመተ ምህረት የማዕከላዊ ስታትስቲክስ መረጃ በ2014 የህዝብ ትንበያ መሰረት የዞኑ ህዝብ 714ሺ 627 ሺ እንደሆነ መረጃው ያሳያል።
በቤንች ሸኮ ዞን ከ17 በላይ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዞኑ የሚገኙ ሲሆን በዞኑ የቤንችና ሸኮ ነባር ብሔረሰቦችም ይገኛሉ።
የቤንች ሸኮ ዞን በ5.33 – 7.21 ላቲቲዩድ ፣ በ34.88 – 36.14 ሎንግቲዩድ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በሰሜንና በሰሜን ምስራቅ ከካፋ ዞን ፣ በሰሜን ምዕራብ ከሸካ ዞን ፣ በደቡብ ምስራቅ ከምዕራብ ኦሞ ዞን ጋር ይዋሰናል።
የቤንች ሸኮ ዞን 127 የገጠር እንዲሁም 21 የከተማ በድምሩ 148 ቀበሌዎችን ይዟል።
የቤንች ሸኮ ዞን ከአመት አመት ዝናብ አይጠፋባቸውም ከሚባሉ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተጠቃሽ ሲሆን ባለው የተፈጥሮ ሀብትና የደን ሽፋን የተነሳ አካባቢው የኢትዮጵያ ሳንባ እየተባለ ይጠራል፡፡የቤንች ሸኮ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ሚዛን አማን የደቡብ ምዕራብ አረንጓዴዋ ፈርጥ ከተማ በመባል የምትታወቅ ሲሆን ከተማዋ በደቡብ ምዕራብ ቀጠና የቱሪዝም ፣ የኮንፍረንስ ቱሪዝምና የንግድ ማዕከል በመሆኗ የከተማዋ የንግድና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዋ ከዓመት ዓመት እያደገ ይገኛል፡፡
የሚዛን አማን ከተማ ህብረ ብሔራዊ ከተማ ከመሆኗ ባሻገር በቅርቡ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የመሰረተ ድንጋይ የተጣለለት የሚዛን አማን ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ኢንቨስትመንቱን በማስፋት ረገድ የጎላ ድርሻ ይኖረዋል፡፡
ከማህበራዊ አገልግሎት ረገድ በትምህርት ዘርፍ በ2016 የትምህርት ዘመን በቅድመ መደበኛ 208 ፣ በ1ኛ ደረጃ 244 እና በ2ኛ ደረጃ 30 ትምህርት ቤቶች በመንግስትና በግል ኢንቨስት ተደርጎ የትምህርት አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል፡፡በጤና አገልግሎት በተገባደደዉ በጀት ዓመት 1 ማስተማሪያ ሆስፒታል ፣ 1 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ፣ 26 ጤና ጣቢያዎች እና 132 ጤና ኬላዎች የሚገኙ ሲሆን የዞኑ አጠቃላይ የጤና ሽፋን 92 በመቶ ነዉ፡፡
በጤናው ዘርፍ በዞኑ 2 ሆስፒታል ፣ 27 ጤና ጣቢያዎች ፣ 138 የጤና ኬላዎች ይገኛሉ። አንድ ሆስፒታል ለ57ሺ 048 እንዲሁም አንድ ጤና ጣቢያ ለ27ሺ 448 እንዲሁም አንድ ጤና ኬላ ለ5ሺ 374 ሰዎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
በዞኑ ሼይ ቤንች ፣ ደቡብ ቤንች እያንዳዳቸው በወረዳቸው 6 ጤና ጣቢያዎችን ያያዙ ሲሆን ጊዲ ቤንችና ሲዝ ከተማ አስተዳዳር እያንዳዳቸው አንድ ጤና ጣቢያ ብቻ ይዘዋል።
በግብርናው ዘርፍ በዞኑ በ2014 በዋና ዋናና በሆርቲካልቸር ሰብሎች ከ220ሺ ሄክታር በላይ መሬት ታርሷል። በዞኑ ሩዝ ፣ ጤፍ ፣ ስንዴ ፣ ገብስ ፣ በቆሎ ፣ ማሽላ ፣ ባቄላ ፣ አተርና የመሳሰሉት በስፋት ይመረታሉ።
በእንስሳት ዘርፍ ከብት ፣ በግ ፣ ፍየል ፣ ዶሮ ፣ አህያ ፣ ፈረስ የሚገኙ ሲሆን የቁም ከብት 1,031,231 ፣ በግ 724,303 ፣ ፍየል 3,321,861 ፣ ዶሮ 2,343,156 ፣ ፈረስ 32,585 ፣ በቅሎ 12,364 እንዲሁም 9,076 አህያ በዞኑ ይገኛል።
በፋይናንስ ደረጃ በዞኑ 2 የመንግስትና ከ19 በላይ የግል ባንኮች የሚገኙ ሲሆን አንድ የመንግስትና 2 የግል የኢንሹራንስ ተቋማትም ይገኛሉ።
ዞኑ ዕምቅ ባህላዊና ተፈጥሮአዊ የቱሪስት መስህቦች የሚገኙ ሲሆን የገበታ ለሀገር አካል የሆነው የደምቢ ሰው ሰራሽ ግድብና ፏፏቴ ፣ የሸኮ ጥቅጥቅ ደን ፣ የሺሚና ኦጀምታ ፍል ውሃ ፣ የሀዝቅን ፣ የሶያና የዲያባትን ዋሻ የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡ መስህቦቹ ለምተዉ ለቱሪዝም አገልግሎት ክፍት ቢሆኑ ለዞኑ ብሎም ለሀገር የሚያስገኘዉ ገቢ ቀላል ባለመሆኑ በዘርፉ ማልማት የሚፈልጉ አካላት ከቤንች ሸኮ ዞን መንግስት ጋር ተቀራርበው እንዲሰሩ እንላለን፡፡
የቤንች ሸኮ ዞን ባለው ምቹ ስነ ምህዳር ፣ ሰፊ ሊለማ የሚችል መሬትና አመቱን ሙሉ የሚፈሱ የገጽ ምድር የውሃ አማራጮች ያሉት በመሆኑ ዞኑ ለኢንቨስትመንት ምቹ ነው፡፡በዚህም በግብርና 90 ፣ በኢንዱስትሪ 73 እና በአገልግሎት 41 በድምሩ 204 ኢንቨስተሮች በዞናችን መጥተዉ 37 ሺህ 230.49 ሄክታር በላይ መሬት ወስደው እያለሙ ይገኛሉ፡፡
ዞኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ቡናን በአልሚ ባለሀብቱና በአርሶ አደሩ ከ140ሺ ሄክታር መሬት በላይ ያለማ ፣ ቅመማ ቅመምና ሰብልን በስፋት የሚያመርት ሲሆን ቡና በአመት ከ65ሺ ቶን በላይ ለማዕከላዊ ገበያ ይቀርባል፡፡በሰብል ረገድ ሩዝን በኢትዮጵያ በስፋት ከሚያመርቱ አካባቢዎች ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ በተለይም በቅባት ሰብሎች ማለትም በሰሊጥ ፣ በማሾ ፣ በቦለቄና መሰል ኤክስፖርት ምርቶች ላይ ለሚሰማሩ አልሚ ባለሀብቶች ዞኑ ሰፊ ሊማ የሚችል መሬት አዘጋጅቶ እየጠበቀ ይገኛል፡፡
በዚህም አልሚ ባለሀብቱ በዘርፉ ከ4.5 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ያስመዘገቡ ሲሆን ለ2ሺ 900 ቋሚና 43ሺ 773 በግዜያዊ የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡
በዞናችን አሁን ላይ በተለያዩ ዘርፎች ያልለሙ 20 ሺ ሄክታር መሬት ለኢንቨስትመንት ያልተላለፈ ሲሆን በተለይም በአግሮ ፕሮሰሲንግና በኤክስፖርት ምርቶች ላይ ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸዉ ሁሉ መጥተዉ ቢያለሙ የዞኑ መንግስት አስፈላጊዉን ሁሉ ድጋፍ ያደርጋል፡፡








Nationalities in Bench Sheko Zone, Bench & Sheko

Bench Nationality

Sheko Nationality
