ከ146 ዓመታት ወዲህ በወርሃ የካቲት 2016 ዓ/ም የሸካቾ ባህላዊ የአስተዳደር መዋቅር ወደ ስራ ከገባ ለመጀመሪያ ጊዜ “ማሽቃሬ ባሮ”የዘመን መለወጫ በዓል በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች ተከብሯል።
ፕሮግራሙ በሚክረቾ አባላት ባህላዊ የምርቃት ስነስርዓት በማድረግ በይፋ ነው የተከበረው። በዘመን መለወጫ ስነስርዓት ላይበመገኘት ንግግር ያደረጉት የአንድራቻ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ አየለ አንገሎ የሸካቾ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ማሽቃሬ ባሮ ” ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በማልማትና በመንከባከብ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ የአሁኑ ትውልድ ትልቅ አደራ ያለበት ነው ብለዋል። የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ዞኑ የኤክስፖርት ምርቶች በስፋት…
