ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፤ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋገጡ
ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን በመጠቀም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ። ከሁለተኛ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ጎን ለጎን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል። ሚኒስትሮቹ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በውይይታቸው አንስተዋል። የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስትር ግርማ…
