ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፤ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያላቸውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ አረጋገጡ

ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በግብርና፣ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ዘርፍ ያሉ አማራጮችን በመጠቀም ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ። ከሁለተኛ የምግብ ስርዓት ጉባኤ ጎን ለጎን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአካባቢና አየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር አምና አልደሃክ (ዶ/ር) ጋር ውይይት አድርገዋል። ሚኒስትሮቹ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ጠንካራና ስትራቴጂካዊ ግንኙነት በውይይታቸው አንስተዋል። የኢፌዲሪ ግብርና ሚኒስትር ግርማ…

Read More

የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ የሥራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የዳውሮ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ የስራ ዘመን 27ኛ መደበኛ ጉባዔ በታርጫ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። በጉባዔው መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዳውሮ ዞን ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ዳዊት ሚኖታ ምክር ቤቶች የህዝብ ሉዓላዊነት መገለጫዎች መሆናቸውን አንስተዋል። በተጨማሪ የዞኑ ምክር ቤት በተጠናቀቀው የበጀት አመት በርካታ ውጤታማ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱንም ገልፀዋል። ጉባዔው ለተከታታይ…

Read More

ህዝቡን ብቃት በማስተባበር በፓርቲ መሪነት ትላልቅ ስኬቶች ተመዝግበዋል ፦አቶ ነጋ አበራ

‎ ‎በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ህብረተሰቡን በብቃት በማስተባበር በፓርቲ መሪነት ትላልቅ ስኬቶች ተመዝግበዋል ሲል የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነጋ አበራ ገለጹ ‎ ‎የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ማጠቃለያ ግምገማ እና የ2018 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ…

Read More

ግልፀኝነት የሰፈነውን ጨረታ ሂደት ለማስፈንና ውጤታማ ግዥ ለማስፈጸም የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ

ግልፀኝነት የሰፈነውን ጨረታ ሂደት ለማስፈንና ውጤታማ ግዥ ለማስፈጸም የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ወሳኝ መሆኑ ተመላከተ የፈደራል ግዥና ንብረት ባለስልጣል ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያዊ ክልል ማዕከል ለተመረጡ ግዥ ባለሙያዎች የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ላይ ስልጠና በቦንጋ ከተማ እየሰጠ ነው። በመክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የክልሉ የመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ የሺሐረግ ደበበ የኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት እኩል የውድድር…

Read More

የካፋ ዞን ምክር ቤት 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 25ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል

ምክር ቤቱ በቅርቡ ላረፉት የምክር ቤት አባል የተከበሩ ሀጂ በድሩዘማን አብደላ ህልፈት የህልና ፀሎት በማድረግ ጉባኤ ተጀምሯል:: ምክር ቤቱ 4ኛ ዙር 12ኛ ዓመት 24ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ- ጉባኤ መርምሮ አፅድቋል። የዞኑ ምክርቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ግርማ ደፋር ለምክር ቤት አባላት የጉባኤ አጀንዳዎችን አቅርበዋል ። በጉባኤው የምክር ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርትና የ2018…

Read More

ቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኮሞሮስ ሕብረት ፕሬዚዳንት አዛሊ አሱማኒ ጋር ተወያዩ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መረጃ ከሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባኤ በፊት፣ ወንድሜን አዛሊ አሱማኒ የኮሞሮስ ሕብረት ፕሬዚዳንት ጋር በሁለትዮሽ እና አህጉራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል ብለዋል።

Read More

ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ መካሔድ ጀመረ

ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ የመክፈቻ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ መካሔድ ጀምሯል። በጉባኤው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የጣሊያን ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ጂኦርጂያ ሜሎኒ፣ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር መሃመድ አሊ የሱፍ ተገኝተዋል። በተመሳሳይ የኬንያ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዊልያም ሩቶ፣ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ፣ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ፣ የላይቤሪያ…

Read More

በአንድ ጀንበር ተከላ ከ21 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2017 ዓ/ም የአንድ ጀንበር ተከላ ክልላዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሀግብር ከ21 ሚሊዮን በላይ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት መደረጉን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ሀላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደተናገሩት የ2017 ክልላዊ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ በዕለቱ ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ከ21 ሚሊዮን በላይ ችግኞች…

Read More