Dawro Nationality
ዳዉሮ ዞን በደቡብ ምዕራብ ዉስጥ ከሚገኙ ስድስቱ ዞኖች አንዱ ነዉ፡፡ ዳወሮ በምእራብ ኮንታ ዞንን፣ጂማ ዞንን /ኦሮሚያ ክልልን፣ በሰሜን ሃዲያ እና ከንባታ ጠንባሮ ዞኖችን፣በሰሜን ምስራቅ ወላይታ እና ጋሞ ዞኖችን ፣በምስራቅ ጎፋ ዞንን ያዋስኑታል፡፡
የዞኑ ቆዳ ስፋት (ሐምሌ 2007፤47) በኢ/ያ ማእከላዊ ስታቲክስ ኤጀንሲ ሰነድ በተጻፈዉ መሰረት 5,225.61 ካሬ ኪ.ሜትር እንደሆነ ተወሰዷል፡፡
ዳዉሮ ዞን እስከ 2010 ዓ/ም ድረስ አምስት ወረዳዎችና አንድ ከተማ አሰተዳደር የነበሩት ሲሆን ከጥቅምት 2011ዓ/ም ጀምሮ አምስት ወረዳዎችና አንድ ከተማ አስተዳደር ተጨምሮ አስር ወረዳ እና ሁለት ከተማ አሰተዳደር አሉት፡፡”
ዳዉሮ ”የሚለዉ ስም የብሔሩና የዞኑ መጠሪያ ሲሆን እንደ ብሔሩ ትርጉም ጀግና፣ጎበዝ፣ታታሪ፣ደፋርና ኩሩ የሚል ስያሜ እንዳለ ይገለጻል. (ተረፈ ገብሬና ሌሎች 1987 ዓ/ም በወንድሙ ልማ እና ሙሉጌታ ዛብህ 2003 ዓ/ም እንደተጠቀሱት
በቋንቁ ቤተሰብ መሠረት ዳዉሮ ” ኦሟዊ ህዝቦች “ ከሚባሉት ዉስጥ ይመደባል፡ቋንቋዉ ዳዉረኛ ስሆን በመላዉ ዞን እና አጎራባች አከባቢዎች ይነገራል፡፡የዞኑ ሕዝብ ብዛት በማእከላዊ እስታትክስ ፕሮጀክሽን መሰረት ከ850 ሺህ በላይ እንደሚሆን ይታመናል፡፡
የዳዉሮ ፖለቲካዊ አስ/ር አደረጃጀትን ስንመለከት በግምት ከ12ኛ ክ/ዘመን በፊት ጀምሮ ራሱን በራሱ የሚያስተዳድር ጠንካራ የአስተዳደር መዋቅር የገነባ ሀገር (STATE/ KINGDOME) ነበር፡፡ ከ16ኛዉ አስከ 19ኛ ክ/ዘ ፖለቲካዊ መዋቅር በማሻሻል ቤተ-መንግስትን ከአሁኑ ዲሳ ወረዳ ኩይሊ ቀበሌ ወደ ደጋዉ ከፍታ ቦታ ሎማ ወረዳ ኮይሻ ካቲ ጋê*ዋ ላይ በማቋቋም 14 የሚሆኑ ነገስታት በካዉካ ሥርወ-መንግስት አሰተዳድረዋል፡፡ዳዉሮ በዳግማዊ ሚኒሊክ ወረራ በ1885ዓ/ም የኢ/ያ ማእከላዊ መንስት አካል ሆኗል፡፡
የዳዉሮ ኢኮኖሚያዊ አደረጃጀት ስንመለከት በዞኑ ዉስጥ ከጥንት ጀምሮ የእርሻ ስራ፤ብረታብረት ስራ፤ማእድናት ማንጠር፤ሸማኔ ስራ ፤የሸክላ ስራ፤ የቆዳ ስራ፤የአናጺነት ስራ፤አደን ማደን፤ ንግድ በስፋት ይከናወናል፡፡ከሙያቸው አንፃር በሳይንሳዊ እይታ የዳውሮ ጥንታዊነት ከሚያረጋግጡት ተግባር አንዱ ደንቻዎች በዋናነት የሚተዳደሩበት በቆዳ ሥራ ነው፡፡ ቆዳን በድንጋይ በመፋቅ (ማንቻላ) ቴክኖሎጂ የጥንት ናይሎቲክ ሥልጣኔ ቴክኖሎጂ ሆኖ ከዓለም የጠፋው ነገር ግን በዳውሮ እስከ ዛሬ በተግባር መታየቱ ጥንታዊ መሠረት እንዳለ የኢንትሮፓሎጂ እና የሶሽዮሎጂ ተመርማሪዎች ይጠቁማሉ ፡፡(ከሉላ ፓንክሬስትና ገብሬ ይንትስ 2007)
በአለም በርዝመት ተወዳዳሪ የሌለዉ የእስትንፋስ ሙዝቃ መሳሪያ ድንካ የዳዉሮ ብሄር ከሚታወቅበት አንዱ ስሆን ለደስታም ሆነ ለሀዘን ዘዉትር ይጠቀማሉ፡፡
ዳዉሮ ለግብርና ስራ ምቹ ከሚባሉ አከባቢዎች አንዱ ስሆን በቆሎ፤አተር ፤ጤፍ ፤ገብስ ፤ማሽላ ፤ስንዴ በብዛት ይመረታል፡፡ u›=d^፣በካጪ፣በዲሳ፣በገና እና ሌሎች ወረዳዎች ሰፊ መሬት ወስደው ባለሀብቶች በግብርና ተሰማርተዉ ይገኛሉ ፡፡ዞኑ በአሁኑ ሰዓት የድንጋይ ከሰልን ለማዕከላዊ መንግስት በከፍተኛ ሁኔት ከሚያቀርቡ አከባቢዎች አንዱ ነው ፡፡
በገበታ ለሀገር የተገነባው የሀላላ ክልስተር የመዝነኛ ሎጂ ለቱርዝም እንቅስቃሴ ምቼ ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል ፡፤በአንድ ረድፍ 175 ኪ.ሜትር እና በአጠቃላይ ርዝመት በሳባት ረድፍ 1225 ኪ.ሜትር የሚሸፍን ከ2.5 እስከ 5 ሜትር ስፋት ከ2.5 እስከ 3.8 ሜትር በላይ ከፍታ ያለው ከ200 አመት በላይ ለግንባታ የፈጀው የንጉስ ሀላላ የጦር መከለካያ ግንብ ሌላኛው የዞኑ ትልቁ ቅርስ ነው፡፡በተጨማሪም በሎማ ኮይሻ ያለዉ የንግሱ ዋናዉ በቴ- መንግሥት፣ በድንጋይ ተበርብሮዉ የተዘጋጀ የቤተ መገለገያ ዕቃዎች፣ በቶጫ ያለዉ አንጋላቲ ጋቤ መደብ፣በኮንታና በዳዉሮ ዞኖች መካከል ያለዉ የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክና ለእይታ ሳቢ የሆኑ የዱር አራዊቶች ፣በጊቤ- 3 ኤለክትሪክ ኃይል ማመንጫ ምክንያት የተፈጠረዉ ሰዉ ሰራሽ ሀይቅ ተጨማሪ ለአከባቢ ኢንበስትመንትና ቱርዝም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከታል፡፡
በዞኑ ዉስጥ 429 መደበኛ ትም/ቤቶች ያሉት ስሆን ከ2 መቶ 50 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ላይ እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
የታርጫ ጠቅላላ ሆስፕታል፣ የቶጫና የገሳ ጫረ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፕታል በዞኑ የጤና አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ሆስፕታሎች ስሆን የዋካ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፕታል በቅርቡ ተመርቆ ለአገልህሎት ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
የታርጫ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ፣የገሳ ጫረ ፣የቶጫ እና የኢሰራ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ፣ የወላይታ ታርጫ ካምፓስ በዞን ዉስጥ አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ከፍተኛ የትም/ት ተቋማት ናቸዉ፡፡

Dawro Nationality














