194 በርሜል ናፍጣ እና ቤንዝል በቁጥጥር ስር ዋለ
የጉራፈረዳ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ቤንዚንና ናፍጣ በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ። በጉራፈረዳ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ኩራቱ በላቸው እንደገለፁት በወረዳዉ በኩጃ ቀበሌ ላይ፣ በተለምዶ አሸዋ ዳጌት ተብሎ በሚጠራው መንደር ሰሞኑን ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት ባደረገው ፍተሻ 194 በርሜል ህገወጥ የነዳጅ ምርት መያዙን ተናግረዋል። 129 በርሜል ቤንዝል እና 65 በርሜል ናፍጣ ፖሊስ…
