




የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቤት በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ በሚዛን አማን ከተማ የሚያካሂደዉ የግምገማ መድረክ ተጠናቀቀ
በመድረኩ ያለፈው 2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ከመገምገም ባሻገር 2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ በመወያየት የቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል።
የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደተናገሩት፤እስካሁን ከመጣንበት ይልቅ ቀጣይ የሚንጓዘዉ ርቀት ውስብስብ እና ፈታኝ ድርብርብ ተልዕኮዎች የሚጠብቁብን ወቅት ላይ እንገኛለን።
ቀጣይ የሚጠብቁብን በርካታ ተልዕኮችን መፈጸም እንዲቻል የአመራሩ እና አባላት የተግባርና የአስተሳሰብ አንድነት በየጊዜው መፍተሽና መገምገም እንደሚገባ ነው አቶ ፍቅሬ አማን ያስገነዘቡት።
በተቋማት፣በአስፈፃሚዎችና በፈጻሚዎች ደረጃ ውጤታማነትን እያረጋገጡ መሄድ ለነገ የማይባል ጉዳይ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ፍቅሬ ለጠንካራ መንግስት ግንባታ ጠንካራ ፓርቲ መገንባት ወሳኝ ጉዳይ ነውም ብለዋል።
በፓርቲው መሪነት የሚወርዱ የኢንሼቲቭ አጀንዳዎችን መከታተልና ውጤታማነቱን መፈተሽ የህዝብን ተሳትፎ ማጠናከርና የህዝቡ የልማት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።
በተያዘዉ 2018 በጀት ዓመት በህልና፣አስተሳሰብ እና በተግባር አንድ በመሆን ከሌሎች ጊዜያት በተሻለ ተልዕኮችን መፈጸም እንደሚገባም አቶ ፍቅሬ አማን አሳስበዋል።
በመድረኩ ማጠቃለያ በክልሉ በሁሉም ዞን መዋቅሮች
በሚገነባው የፓርቲ ጽ/ቤት ህንጻ ግንባታ ዙሪያ ውይይት ተደርገው የግብ ስምምነት ተፈጽሟል።
በተጨማሪም በ2017 በጀት ዓመት በተለያዬ መመዘናዎች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ዞኖች እውቅና እና ማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
የተሰጠው እውቅና እና ማበረታቻ ለቀጣይ ተልዕኮ መነሳሳትን የሚፈጥር፣ተቀራራቢ ውጤት ለማስመዝገብ ጤናማ ፉክክር የሚያሳድር እንዲሁም የተግባራትን ውጤታማነት የሚያሳድግ መሆኑም ተመላክቷል።
በፍቅር ከበደ
