ክልሉ 21 ሺህ 877 ቶን ቅመማቅመም ለማዕከላዊ ገበያ አቀረበ
21 ሺህ 877 ቶን ቅመማቅመም ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡ የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር እና የቡና፣ ሻይና ቅመማቅመም ልማትና ጥበቃ ዘርፍ ኃላፊ አቶ በላይ ኮጁአብ÷ ክልሉ ለቅመማቅመም ልማት ቢያመችም የህግ ማዕቀፍ እና ወጥነት ያለው የግብይት ስርዓት አለመኖር ያለውን አቅም አሟጦ ለመጠቀም እንዳላስቻለ ገልጸዋል። ይህ እንዳለ ሆኖ ክልላዊ የቅመማቅመም…
