የአዲስ አበባ የለውጥ ጉዞ አስደንቆኛል- ዌላርስ ጋሳማጌራ

አዲስ አበባ በአስደናቂ የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ መመልከታቸውን የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ዌላርስ ጋሳማጌራ ገለጹ። የሩዋንዳ አርበኞች ግንባር ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ዌላርስ ጋሳማጌራ የአንድነት ፓርክን ጎብኝተዋል። ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ” ከቃል እስከ ባህል ” በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 23 እስከ 25 በአዲስ አበባ ያካሄዳል። በጉባኤ ላይ ለመታደም አዲስ አበባ ከገቡ የውጭ…

Read More

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ጂማ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት በቤንች ሸኮና ሸካ ዞኖች ግማሽ ሚሊየን ብር የሚጠጋ የተበላሹና የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ምግብና መጠጦችን ማስወገዱን አስታወቀ።

ህብረተሰቡ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸውና ባዕድ ነገር የተቀየጡ ምግቦችን ሲመለከት በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የጸጥታ አካላትና በ8284 በነጻ በመደወል ጥቆማ መስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከኢትዮጵያ የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን ጂማ ቅርንጫፍ ጋር በመቀናጀት በቤንች ሸኮ እና ሸካ ዞን በምግብና መጠጥ አከፋፋዮችና የችርቻሮ ሱቆች የክትትልና የቁጥጥር ስራ መስራቱን ገልጿል። በክልሉ ጤና ቢሮ የጤናና ጤና…

Read More

ምክር ቤቱ የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አጽድቋል፡፡ የረቂቁን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡ ረቂቅ አዋጁ ትምህርትን በእኩልነት እና ፍትሃዊነት በመላ ሀገሪቷ ተደራሽ ለማድረግ የጎላ ሚና እንዳለው ሰብሳቢው አብራርተዋል፡፡ እንዲሁም፣ ረቂቅ አዋጁ የመምህራንን ጥራት…

Read More

አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ

አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር በመሆን በምክር ቤቱ ተሹመዋል። ለሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮምሽነር በመሆን የተመረጡት አቶ ብርሃኑ በጉባዔው ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል።

Read More

በምዕራብ ኦሞ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በጋችት ወረዳ በይፋ ተጀመረ

በምዕራብ ኦሞ ዞን የዘንድሮው የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ሥራ በጋችት ወረዳ ቤሩ ቀበሌ የክልል እና የዞን የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ዞናዊ ማስጀመሪያ በዛሬ በይፋ ተጀምሯል። የተፋሰስ ልማት ሥራው “የአፈር ጥበቃ ስራችን ለብልፅግናችን” በሚል መሪ ሃሳብ በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች ላይ እየተካሄደ መሆኑ ተገልጿል። የክልል እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ የወረዳ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች የተፋሰስ ስራዎችን አስጀምረዋል።…

Read More

የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ከሞሮኮው አር ኤን አይ ፓርቲ ተወካይ ጋር ተወያዩ

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ከሞሮኮው ናሽናል ራሊ ኦፍ ኢንዲፔንደንትስ (አር ኤን አይ) ፓርቲ ተወካይ ፕሮፌሰር መሀመድ ሳዲኪ ጋር ተወያይተዋል። የሞሮኮ ናሽናል ራሊ ኦፍ ኢንዲፔንደንትስ ፓርቲ ተወካይ ፕሮፌሰር መሀመድ ሳዲኪ በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለመታደም ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ መግባታቸው ይታወሳል። በዛሬው…

Read More

በኮንታ ዞን የአፈርና ውሃ ጥበቃ ልማት ስራ በይፋ ተጀመረ።

ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ ስራዎች የተገኙ ተሞክሮዎችን በማጠናከር ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር በተቀናጀ መንገድ ሊሰራ እንደሚገባ ተገልጿል። በዞኑ የ2017 ዓ.ም የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራ “የአፈር ሀብታችን ለብልጽግናችን” በሚል መሪ ሀሳብ በአመያ ከተማ አስተዳደር ጨካ ቦቻ ቀበሌ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የዞኑ ም/ል አስተዳዳሪና የገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድማገኝ ወጁ የተፋሰስ ልማት ስራ የመሬት…

Read More

ብልጽግና ፓርቲ ሁሉንም በእኩልነት የሚያሳትፍና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን እውን የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ አድርጓል – የፓርቲው አመራሮች

ብልጽግና ፓርቲ ሁሉንም በእኩልነት የሚያሳትፍና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን እውን የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ማድረጉን የፓርቲው አመራሮች ገለጹ። የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 በአዲስ አበባ ይካሄዳል። በፓርቲው የመጀመሪያው ጉባኤ የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና እድገት የሚያፋጥኑ ተግባራትን ለማከናወን ቃል መገባቱ ይታወሳል። የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና የሚያረጋግጡ ውሳኔዎችን በማሳለፍም ለተግባራዊነቱ በስፋት መስራት ተችሏል። በዚህም የተባበረ…

Read More

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የ2017 ዓ.ም

የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በይፋ ተጀመረ የ2017 ምርት ዘመን ክልላዊ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ማብሰሪያ ፕሮግራም በካፋ ዞን፣ ሺሾ እንዴ ወረዳ፣ ዳኼራ ቀበሌ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተገኙበት በይፋ ተከናውኗል። መርሐ ግብሩን በይፋ ያስጀመሩት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድ የኢኮኖሚና መሰረተ ልማት ዘርፍ አማካሪ ዶ/ር ኢንጂነር ምትኩ በድሩ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና ልማት…

Read More

በቤንች ሸኮ ዞን ዞናዊ የተፋሰስ ልማት ስራ በሁሉም መዋቅሮች ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ እየተሰራ ነው

የክልል ፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በሼይ ቤንች ወረዳ ማዝ ቀበሌ ሺንክ ንዑስ ተፋሰስ በይፋ ተጀምሯል። የቤንች ሸኮ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን መንገሻ የተፋሰስ ልማቱን በይፋ ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት የአፈር ሀብታችንን መጠበቅ ሰውን ፣ እንስሳትንና የውሀ ሀብታችንን መጠበቅ በመሆኑ ዘንድሮ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል። የተፋሰስ ልማት ለበርካታ…

Read More