Konta Nationality in Konta

Konta Nationality
የኮንታ ዞን መሰረታዊ መረጃ (ዳራ)
የዞኑ መሰረታዊ መረጃ (ዳራ) የኮንታ ዞን በአዲስ መልክ ወደ ዞን መዋቅር ከማደጉ በፊት የልዩ ወረዳነት መዋቅር ያገኘው በቀድሞ ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት በነበረበት ወቅት በህዳር 1993 ዓ.ም ሲሆን ወደ ዞን መዋቅር ዕዉቅና አግኝቶ ያደገው በአዲሱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት መስራች ጉባኤ ህዳር 14/2014 ዓ/ም ነዉ፡:የኮንታ ዞን በ6.46′-7.26′ ሴሜን ላቲቲዩድ’’ እና በ36.32-36.87 ምስራቅ “ሎንግቲዩድ” መሥመሮች ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በስተሰሜን በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከጅማ ዞን ዴዶ እና ማንቾ ወረዳ፣በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በከፋ ዞን፣ በስተምዕራብ ጨታ፣ዴቻ፣ጠሎና አዲዮ ወረዳ፣በምሥራቅ ከዳውሮ ዞን ታርጫ ዙሪያ፣ቶጫ፣ኢሰራ ወረዳ፤በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል መንግስት በደቡብ ኦሞ ዞን ከሰላማጎ ወረዳ፣ በስተደቡብ ምሥራቅ ከጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ የሚዋሰን ሲሆን የዞኑ ዋና ከተማ አመያ ነዉ፡፡ በዞኑ ሥር ሦስት ወረዳዎች፣ሁለት የከተማ አስተዳደር መወቀቅሮች፣አምስት ማዘጋጃ ቤቶችና በ17 የከተማ እና በ45 የገጠር ቀበሌዎች በድምሩ በ62 ቀበሌ መዋቅሮች የተከፋፈለ ነዉ። ከዞኑ ዋና ከተማ መነሻ አንስቶ ከአገሪቱ ርዕሰ መዲና ከአዲስ አበባ- ጂማ-አመያ 465 ኪሎ ሜትር፣በቦንጋ-አመያ-ጂማ በኩል 225 ኪሎ ሜትር ሲሆን ቦንጋ ፈለቀ ሰላም-አመያ 109 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል።mአጠቃላይ የዞኑ ቆዳ ስፋት 238,163 ሄክታር ሲሆን መልከዓ ምድራዊ አቀማመጡ 28% ሜዳማ፣ 38.5% ተራራማ እና 33.5% ተዳፋታማ ነው። 1.1የዞኑ አየር ንብረትን ሁኔታን በተመለከተ፤- ዞኑ የበልግና የመኸር ዝናብ ተጠቃሚ ሲሆን ከፍተኛው የዝናብ መጠን 2,290 ሚ.ሜ ሲሆን ዝቅተኛው 1,200 ሚ.ሜ ሆኖ አማካይ የዝናብ መጠን 1,745 ሚ.ሜ ይደርሳል።እንዲሁም የዞኑ አማካይ የሙቀት መጠን 25.5 ዲግሪሴንቲግሬድ ይሆናል።ዞኑ ከባህር ወለል በላይ ያለው ከፍታ ከ790 ሜትር እስከ 2,750 ሜትር ይሆናል። አየር ንብረት ደጋማ ክፍል 6%፣ወይናደጋ 54% እና ቆላ 40% ይሸፍናል። በኮንታ ዞን የተለያዩ የኢትዮጵያ ብሔሮችና ብሔረሰቦች የምኖሩበት አካባቢ ሲሆን በዋናነት ነባሩ የኮንታ ብሔረሰብ ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ሌሎች የዳዉሮ፣የካፋ፣የኦሮሞ፣የአማራ እና ሌሎችም ብሔረሰብ አባላት ከረዥም ጊዜ አንስቶ ከነባሩ ብሔረሰብ ጋር በፍቅር ይኖራለ፡፡መንግስት የገጠር ማህበረሰብን የምግብ ዋስትና ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በነደፈዉ የሰፈራ ፕሮግራም ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወላይታ እና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሀድያ ዞን ብሔረሰብ ተወላጆች በዞኑ በኮንታ ኮይሻ ወረዳ ውስጥ ሰፍረዉ ይገኛሉ፡፡ይህም ዞኑን የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦች መኖሪያ እና አብሮ ተቻችለው የምኖሩበት ትንሹ ኢትዮጵያ ያደርገዋል፡፡ 1.3 ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶች፤- ዞኑ የተለያዩ ባህላዊና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን የታደለ ሲሆን ከባህላዊ ሀብቶች አንፃር የብሔረሰቡ ዘመን መለወጫ ስርዓት (Hingicaa)፣አባቶች በቀደሙት ዘመናት ከአጎራባች አካባቢዎች ጋር ባደረጉት ወረራ የብሔረሰቡን ድንበር ለማስጠበቅ የቆፈራቸዉና ዞኑን እንደመቀነት የዞረዉ የጦር ጉድጓድ (Boohuwa)፣ከአፈር ብረት የሚመረትበት ባህላዊ የብረት ማቅለጫ ዘዴ፤በሀዘንና በደስታ ጊዜ የሚገለገሉባቸዉ መገለጫዎች እንደ ለቅሶ፤ሰርግ፣ጭፈራ ስነ-ስርዓቶች፣ባህላዊ የመዚቃ መሳሪያዎች፣ምግቦችና መጠጦች የሚጠቀሱ ሲሆን ከተፈጥሯዊ ሀብት አንፃር የጨበራ ጩረጩራ ብሔራዊ ፓርክና በዉስጡ የሚገኙ የተለያዩ የእንስሳትና አዕዋፍ ዝሪያዎች፤ለመጠጥና ለመዲኃኒትነት አገልግሎት የሚዉል ፍልዉሃዎች፤ፋፋቴዎች፣ዋሻዎች፣ሀይቆች፣የተፈጥሮ ማዕድናት እንደ ድንጋይ ከሰልና የብረት ማዕድን፣ጥቅጥቅ ያለ ጥብቅ የተፈጥሮ ደንና የጫካ ቡና በከፊል የሚገለፁ ናቸዉ፡፡የኮንታ ህዝብ መተዳደሪያና የገቢ ምንጭ በዋናነት ጥምር ግብርና ሲሆን የንግድና ሌሎች የዕደጥበብ ስራዎችም አንድ አካል ነው፡1.4 ኢንቨስትመንት፤-ከኢንቨስትሜንት አኳያ ዞኑ በሁሉም ዘርፍ ለኢንቨስትመንት ሰፊ የመልማት አቅም ያለው በተለይም በግብርና ዘርፍ፣ በሆቴልና ቱርዝምና በሌሎችም ዘርፍ ሰፊ potential ያለው ነው፡፡ ከዚህ መነሻ በግብርናና በሆቴል ቱርዝም ዘርፍ በርካታ ባለሀብቶች በመሰማራት ውጤት እያስመዘገቡም ይገኛሉ፡፡በዞኑ አሁን ላይ የገበታ ለሀገር ኮይሻ ፕሮጀክትና ሲጠናቀቅ 2,170 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚችል የኮይሻ ኃይድሮ ኤሌክትሪክ ፓወር ግንባታ እየተገነባ ይገኛል፡፡
Cultural Images Of Konta Nationality









