ተጠናቅቆ ለአገልግሎት የበቁና ቀጣይ የሚገነቡ ፕሮጀክቶች የብልጽግና ፓርቲ ለህዝብ ጥያቄ የሰጠዉ ምላሽ ማሳያ ናቸዉ፦ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)
የህዝብን የልማት ጥያቄ በተገቢው መንገድ ለመመለስ በክልሉ መንግስት የተጀመሩ የተለያዩ ልማት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ተናግረዋል። ርዕሰ መስተዳድሩ ይህንን የገለጹት በዳውሮ ዞን ኢሳራ ባሌ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግንባታ መሠረተ ድንጋይ ባኖሩበትና ግንባታው የተጠናቀቀውን የተለያዩ የልማት ስራዎችን መርቀው በከፈቱበት ወቅት ነው። ባለፉት ዓመታት የተሰጡ የቤት ስራዎች ተጠናቅቆ እየተመረቁ መሆኑን ያመለከቱት ርዕሰ መስተዳድሩ የተጀመሩ…
