በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በክልሉ መጠነ ሰፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ አግኝተዋል። አቶ ፍቅሬ አማን

በብልጽግና ፓርቲ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቅ/ጽ/ቤት የ2017 ዓ/ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ በአማያ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የአፈፃፀም ግምገማ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍቅሬ አማን በብልጽግና ፓርቲ መሪነት በክልሉ መጠነ ሰፊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። አቶ ፍቅሬ፥ ፓርቲው በክልሉ የህዝቡን የልማት፣ የመልካም አስተዳደር እና…

Read More

4 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር የተመደበለት የታርጫ ጪዳ ሎት 3 አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ።

የመንገድ ፕሮጀክቱ 64.8 ኪሎሜትር ርዝመት እንዳለውም ተገልጿል ። የታርጫ ጪዳ መንገድ ተጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ተቋርጦ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ መሰንበቱ ይታወሳል። ይህንን ፕሮጀክት ዳግም መጀመሩን በማስመልከትም ንግግር ያደረጉት ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ የመንገድ ፕሮጀክቱ ተጀምሮ መቋረጡ የአካባቢውን ህብረተሰብ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን በእጅጉ የጎዳ መሆኑን አስታውሰዋል። የብልጽግና ፓርቲ እና መንግስት ይህንን የህዝቡን የመልካም…

Read More

የሥራና ክህሎት ቢሮ ”ብሩህ አዕምሮዎች፤በክህሎት የበቁ ዜጎች በሚል መሪ ቃል የክህሎት፤ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና ኤግዚቢሽን ቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነዉ።

በውድድርና ኤግዚቢሽን መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ እንደገለጹት፤ በፊት ለቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጠዉ ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ በዘርፉ ውጤት ተገቢዉ ዉጤት ሳይመዘገብ ቆይቷል ብለዋል። ለዚህም የተጀመሩ የተቋማት ግንባታዎች ተጠናቅቀዉ አገልግሎት ባለመስጠታቸውና ተቋማት በሚፈልገው ልክ ቴክኖሎጂ ከማሸጋገር አንጻር የነበራቸው ውስንነቶች ተግዳሮት እንደነበርም አስታውሰዋል። ዋና አፈ-ጉባኤው…

Read More

የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ግንባታ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻችንን ይፈታል – የአካባቢው ነዋሪዎች

የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ግንባታ ዳግም መጀመሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮቻቸውን እንደሚፈታላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። የፌደራልና የክልል አመራሮች በተገኙበት ተቋረጦ የነበረው የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ሥራ ትናንት ተጀምሯል። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2010 ዓ.ም ግንባታው ተጀምሮ በሥራ ተቋራጭ አቅም ማነስ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ዳግም ሥራ መጀመሩ የአካባቢውን ህብረተሰብ…

Read More

መምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው – ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር)

ኢትዮጵያ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ በማሻሻል እና የመምህራንን አቅም በመገንባት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረገች መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ገለጹ። የትምህርት ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካን ብሬይን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ‘በ21ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካን ማስተማርና ማብቃት’ በሚል መሪ ሃሳብ ለሶስት ቀናት የተካሄደው ኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል። በዚህ…

Read More

የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ በይፋ ይከፈታል

የ2017 ዓ-ም ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ በአዲስ አበባ በይፋ እንደሚከፈት የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ኤክስፖውን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች ያጋጥማቸው የነበሩ ችግሮች ደረጃ በደረጃ እንዲፈቱና የማምረት አቅማቸው እንዲጎለብት ማድረጉን አንስተዋል። ንቅናቄው የአገር ውስጥ ምርት አጠቃቀም ላይ ሰፊ ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸዋል። 3ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪው ቅዳሜ ሚያዝያ…

Read More

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት እንድትቀላቀል አሜሪካ ድጋፍ ታደርጋለች፦የአሜሪካ የንግድ ፅ/ቤት

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት እንድትቀላቀል አሜሪካ ድጋፍ እንደምታደርግ ገለጸች። ከ2025 የዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋም እና የዓለም ባንክ የጸደይ ስብሰባዎች ጎን ለጎን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በአሜሪካ የንግድ ፅ/ቤት የዓለም ንግድ ድርጅት እና የባለብዙ ወገን ጉዳዮች ረዳት ተወካይ ከሆኑት ኒል ጄ ቤክ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅትን በአባልነት ለመቀላቀል እያደረገች ያለውን…

Read More

በእንቁላል ጣይ ዶሮ እርባታ ውጤታማ መሆናቸውን የታርጫ ከተማ ወጣቶች ተናገሩ ።

በታርጫ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ ያሉ የልማት ስራዎችን ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ወጣቶቹ በተሰማሩባቸው የእንቁላል ጣይ ዶሮ በቀን ከ450 በላይ እንቁላል እያገኙ መሆናቸውን ለርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል ። በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከሚገኙ ዞኖች አንዷ በሆነችሁ ዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር የሌማት ትሩፋት ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የሌማት ትሩፋት አካል የሆነው የእንቁላል ጣይ…

Read More

የመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት የመንግስትን የአገልግሎት አሰጣጥ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑን የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴን ጨምሮ የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን ጎብኝተዋል። መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተመርቆ ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል። ማዕከሉ 12 ተቋማትን እና ከ41 በላይ አገልግሎትን በአንድ ህንፃ ማግኘት የሚያስችል ነው። የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ እንዲሁም የተለያዩ አገራት አምባሳደሮች መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫን…

Read More

የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ታሳቢ ያደረጉ ተግባራት እየተከናወኑ ናቸው፦ የተከበሩ አቶ መቱ አኩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት 3ኛ ዙር 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል። በመድረኩ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤቱ የተከበሩ ዋና አፈ-ጉባኤ አቶ መቱ አኩ ጉባኤው ያለፉትን የ9 ወራት አፈፃፀም በመገምገም ለቀጣይ በቂ ግብአት የሚወሰድበት መሆኑን ገልፀው ምክር ቤቱ ህገ መንግሥታዊ ተልዕኮውን አንግቦ የክልሉን ህዝብ መብትና ጥቅም በማስከበር ረገድ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ…

Read More