ለአመታት ተቋርጦ የነበረው የዲሪ ማሻ አስፋልት መንገድ ስራ እንደገና ሊጀመር ነው ።
ለአመታት የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ የሰነበተው የዲሪ_ማሻ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ እንደገና ወደ ስራ የማስገባት ስነስርዓት በካፋ ዞን ጊንቦ ወረዳ ይደረጋል። ይህንን ስነ _ስርዓት ለማስጀመር የኢፌዴሪ ከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አለማየሁ አየለ የተገኙ ሲሆን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አቀባበል አድርገውላቸዋል።…
