




በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ሻቻ ቀበሌ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸውን ችግኞችን በማፍላት በየዓመቱ ለተቋማትና ለአርሶ አደሮች በማዳረስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ እያበረከተ ያለው ጣቢያ ነዉ።
ችግኝ ጣቢያው የኢኮኖሚ አቅምን ከመገንባት በተጨማሪ በሥራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ ድርሻ እየተወጣ ይገኛል።
ይህን መነሻ በማድረግ በአሁን ወቅት በተለያዩ ፕሮጀክቶች ድጋፍ በ4 ነጥብ 9 ሚሊየን በሚጠጋ በጀት ድጋፍ ችግኝ ጣቢያው የዘመናዊ ሼድ እየተሠራ እንደሚገኝ የጨና ወረዳ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
