የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የአካባቢን ጸጋ መሰረት አድርጎ በመተግበሩ ውጤት እየተመዘገበ ነው::

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልሎች የአካባቢን ጸጋ መሰረት በማድረግ ለሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በተከናወኑ ሥራዎች ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑ ተገለጸ። ከኢዜአ ጋር ቆይታ ያደረጉት የክልሎቹ የሥራ ሃላፊዎች እንደገለጹት መርሀ-ግብሩ የአካባቢን ፀጋ መሠረት ባደረገ መልኩ ተግባራዊ በመደረጉ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡ ናቸው። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር እንደገለጹት ሀገራዊው የሌማት…

Read More

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ የተመድ ዋና ጸሀፊ ልዩ ተወካይና ዩኤንሶም ሀላፊ ጋር ተወያዩ::

የኢፌዲሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ ልዩ ተወካይና በተባበሩት መንግስታት የሶማሊያ ድጋፍ ተልዕኮ(ዩኤንሶም) ሀላፊ ካትሪዮና ላንግ ጋር ተወያዩ፡፡ በውይይታቸውም አምባሳደር ታዬ፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ቀጣይነት ያለው ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ያላትን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል፡፡ ካትሪዮና ላንግ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ ለሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ያደረገችውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድንቀዋል፡፡ በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት ሁለቱ ወገኖች በቀጣይ…

Read More

በምንዛሬ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር ማዳን ተቻለ::

ወደ ሀገር ውስጥ በውጪ ምንዛሬ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር በቀል ምርቶች በመተካት 3 ነጥብ 1 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ከብክነት ማዳን መቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ የ2016 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀምን በተመለከተ ከሚኒስቴሩ ሥራ አስፈፃሚዎች እና ሠራተኞች ጋር እየተወያየ ነው፡፡ በዚህ ወቅትም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ከፍተኛ ጥረት በመደረጉ አበረታች ለውጥ መምጣቱ ተገልጿል።…

Read More

የመከላከያ መረጃ ዋና መምሪያ አዲስ አርማ ይፋ አደረገ::

አዲሱ አርማ ዋና መምሪያው የተሰጠውን ተቋማዊ ግዳጅና ተልዕኮ በሚገልፅ መልኩ ተሰርቶ ርክክብ መደረጉ ተጠቅሷል። በርክክብ ሰነ- ሰርዓቱ ላይ የተገኙት ጀኔራል ጌታቸው ጉዲና ለተቋማዊ ዝማኔም ይሁን ለመምሪያው የግዳጅ አፈፃፀም ውጤት አዲስ የተሰራው አርማ /ሎጎ/ ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል። መለያ ምልክቱን ለማሰራት ሰፊ ጥናት የተካሄደ መሆኑን የተናገሩት ጀኔራል መኮንኑ አርማው በጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዡር ሹም ፊልድ ማርሻል…

Read More

በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ከ50 ሺ በላይ ለሚሆኑ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና ይሰጣል- ትምህርት ሚኒስቴር::

በዘንድሮው ዓመት በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የመምህራን የክረምት ስልጠና ከ50 ሺ በላይ መምህራንና የትምህርት አመራሮች ስልጠና እንደሚሠጣቸው ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት ስልጠናው አሁን እያስተማሩ ያሉ መምህራን በሚያስተምሩት የትምህርት ይዘትና የማስተማሪያ ስነ ዘዴ ላይ ክህሎት እንዲይዙ ያለመ ነው። መምህራኑ በሚያገኙት ስልጠና በሚያስተምሩት ትምህርት ላይ በበቂ ሁኔታ ማስተማር የሚያስችላቸውን ክህሎት እንደሚያገኙ መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።…

Read More

በ2017 በጀት ዓመት በክልሉ ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ገለፀ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የመደበኛ እና ካፒታል በጀት ዕቅድ ላይ ከክልሉ ግብርና ቢሮና ተጠሪ ተቋማት ጋር የበጀት ሰሚ የምክክር መድረክ በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ የክልሉ ግብርና ቢሮና ተጠሪ ተቋማት አጠቃላይ ለ2017 በጀት ዓመት ለሰው ሃይል፣ ለመደበኛ ስራ ማስኬጃ እና ለካፒታል የሚሆን የበጀት ዕቅድ አቅርበው ውይይት ተደርጓል፡፡ በየበጀት ዓመቱ…

Read More

የጠቅላይ ሚኒስትሩ “ጽዱ አካባቢ ለሀገር ግንባታ” ኢኒሼቲቭ ምንድን ነው::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ወደ ሥልጣን ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ እየሠሯቸው ካሉት ሥራዎች መካከል ጽዱ ቢሮን፣ ጽዱ ከተማን እና ጽዱ ሀገርን መፍጠር አንዱ ነው፡፡ “ከቢሮ፣ ግቢ፣ ሠፈር እስከ ሀገር” ብለው ከጽ/ቤታቸው የጀመሩት ይህን እንቅስቃሴ ከአዲስ አበባ አልፎ ወደ ተለያዩ የክልል ከተሞች እያደገ ሀገር አቀፍ ሆኗል፡፡ ሰው አካባቢው ጽዱ ከሆነ መልካም ነገርን የማሰብን ኃይል ያገኛል የሚሉት…

Read More

በክልሉ ክላስተር ከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ የተለያዩ ደረጃ ያላቸዉ ህንጻዎች ልገነቡ ነው::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት በክልሉ ክላስተር ከተሞች ደረጃቸውን የጠበቁ ባለ ዘጠኝ ወለል ህንጻዎችን ለማስገንባት በተዘጋጀው ዲዛይን ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር መከረ። የክልሉ መንግሥት በክላስተር ከተሞቹ ለሚስገነቧቸው ህንጻዎች የዲዛይን ስራውን በኢትዮጵያ ግንባታና ዲዛይን ስራዎች ኮርፖሬሽን ማሰራት ተገልጿል። የግንባታ ዲዛይንና ቁጥጥር ስራው አዲስ በተቋቋመው የመንግስት የልማት ድርጅት በሆነው የደቡብ ምዕራብ ዲዛይን ግንባታ ቁጥጥር ኮርፖሬሽን እና…

Read More

የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ 62 በመቶ መጠናቀቁ ተገለጸ::

የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ 62 በመቶ መጠናቀቁን ግንባታውን የሚያከናውነው ሥራ ተቋራጭ አስታወቀ። የአውሮፕላን ማረፊያውን በተያዘለት ግንባታ ለማጠናቀቅ የአካባቢው የአየር ጸባይ ፈተና መሆኑን ተቋራጩ ገልጿል። የሳምሶን ቸርነት ስራ ተቋራጭ ስራ አስኪያጅ እንጂነር ኢዮብ ሞላ በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች እንደገለጹት፣ የአውሮፕላን ማርፊያው በ930 ሚሊዮን ብር በጀት እየተገነባ ነው። የአውሮፕላን ማረፊያው ከፍተኛ የህዝብ የልማት ጥያቄ…

Read More

በክልሉ ከ68 ሚሊየን ብር በላይ ከምዝበራ ማዳን መቻሉ ተገለጸ::

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በተከናወነ ሙስናን የመከላከል ጥረት ከ68 ሚሊየን ብር በላይ የመንግሥትና የህዝብ ሃብት ከምዝበራ ማዳን መቻሉ ተገልጿል፡፡ የክልሉ ሥነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሽ ኮሚሽነር ሙሉሰው ዘውዴ÷ የመንግሥት ተቋማትና ህዝባዊ የልማት ድርጅቶች ከሙስናና ብልሹ አሰራር በፀዳ መልኩ ሥራቸውን እንዲያከናወኑ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል። ኮሚሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ባደረገው ጥረት በአስቸኳይ ሙስና መከላከል ስራ…

Read More