ውስን የሆነውን ሀብት እና ውድ ጊዜያችንን በአግባቡ ለመጠቀም ተግባራትን በቴክኖሎጂ አስደግፎ ማከናወን እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ምክትል አፌ ጉባኤ አሳሰቡ።

የክልሉ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ የክልሉን የቪዲዮ ኮንፈራንስ አገልግሎት ይፋዊ ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሄዷል። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ክህሎትና ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊና የዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ቤተልሔም ዳንኤል የዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎት መጀመር ለክልሉ መንግሥታዊ አገልግሎት ውጤታማነት ፋይዳው የላቀ ይሆናል ብለዋል። የቪዲዮ ኮንፈንስ አገልግሎቱ የመረጃ ልውውጥ ሂደትን የሚያቀላጥፍ ብሎም ጊዜ እና ሀብትን የሚቆጥብ ተመራጪ ቴክኖሎጂ መሆኑንም ኃላፊዋ…

Read More

ክልሉ ያለዉን እምቅ አቅም ተጠቅሞ በዜጎች ስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ማድረግ አለበት:-የሱፐርቪዥን ቡድን::

የኢፌዲሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን ላለፉት 10 ቀናት በክልሉ ያካሄደውን ድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ግብረ- መልስ ማጠቃለያ ውይይት በቦንጋ ከተማ አካሂዷል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ በክልሉ በወጣቶች ስራ ዕድል ፈጠራ ዘርፍ የተሰሩ የተገኙ ውጤቶች ለማስቀጠል ክህሎት መር ተቋማዊ ግንባታ በማጠናከር በየአካባቢ ተገንብተው ወደስራ ያልገቡ የማምራቸ እና መሸጫ ሼዶችን አጠናቆ ወደ ስራ ማስገባት…

Read More

ሀገራዊ የኮሙኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን በብቃት ለመምራት የዘርፉን ባለሙያዎች አቅም የማሳደግ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል – ዶክተር ለገሰ ቱሉ::

ሀገራዊ ተልዕኮን በአግባቡ የተረዳና በእውቀት የሚመራ የኮሙኒኬሽን እና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያን ለመፍጠር የአቅም ግንባታ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ ገለጹ፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለፌዴራል እና ለክልል የህዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ሲሰጠው የቆየው ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል። የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶክተር ለገሰ ቱሉ በዚሁ ወቅት እንዳሉት ስልጠናው በአምስት ርእሰ…

Read More

ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራር የብቃት ስልጠና ሊሰጥ ነው::

በመጪው ክረምት ለ50 ሺህ መምህራንና የትምህርት አመራሮች የብቃት ስልጠና እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል ። ስልጠናው የትምህርት ጥራት ችግርን ለመቅረፍና የመምህራን ብቃትን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን÷ በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች ይሰጣል ነው የተባለው። በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራን እና የትምህርት አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ(ዶ/ር) መምህራኑ የሚሰለጥኑት በሚያስተምሩት ትምህርትና በማስተማሪያ ዘዴዎች መሆኑን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል ። ለ42 ሺህ…

Read More

የግብርናው ዘርፍ ላይ መዋቅራዊ ሽግግር በማድረግ ድህነትን መቀነስ የመንግስት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ነው – አቶ ተመስገን ጥሩነህ::

የግብርናው ዘርፍ ላይ መዋቅራዊ ሽግግር በማድረግ ድህነትን መቀነስ የመንግስት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ። ሀገራዊዉ የሌማት ትሩፋት የአንድ ዓመት ተኩል አፈፃፀም የግምገማ መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ግብርናውን ከበሬ እርሻ ወደ ተቀናጀ ግብርና ቴክኖሎጂ ለማሻገር ከመንግስት ባለፈ የግሉ ዘርፍ እና ምርምሩ…

Read More

ስታርት አፖችን በፋይናንስ መደገፍ የሚያስችሉ አሠራሮች ተዘርግተው ተግባራዊ እየተደረጉ ነው – የኢትዮጵያ ልማት ባንክ::

በኢትዮጵያ በስፋት የተጀመሩ ስታርት አፖችን በፋይናንስ መደገፍ የሚያስችሉ አሠራሮች ተዘርግተው ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስታወቀ። በሳይንስ ሙዚየም የተከፈተውን ስታርት አፕ ኢትዮጵያ አውደ-ርዕይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ጨምሮ በርካታ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ምሁራንና ተማሪዎች እንዲሁም የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጎብኝተውታል። ከመጋቢት 30 እስከ ሚያዝያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ለሕዝብ ዕይታ ክፍት በተደረገው አውደ-ርዕይ በመጀመሪያ ደረጃ…

Read More

ስፖርት ለአካላዊ ብቃትና ለአዕምሮ ጤንነት የጎላ ሚና እንዳለው የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ ተናገሩ::

መላው የካፋ ዞን እግር ኳስ ክለቦች ጨዋታ በቦንጋ ሁለገብ ስታዲየም ተጀመረ። የ2016 ዓ.ም መላው የካፋ ዞን የእግር ኳስ ክለቦች ጨዋታ በቦንጋ ሁለገብ ስታዲየም የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ጀምሯል። የሠላም ተምሳለት፣የአረንጓዴ ፈርጥ እና የክልሉ የፖለቲካና የአስተዳደር መቀመጫ ቦንጋ ከተማ እንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት የቦንጋ ከተማ ከንቲባ አቶ አስማማው…

Read More

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በማጠናከር የወጣቶችን ስብዕና ግንባታ ማሳደግና ስራ ዕድል ፈጠራ ማሻሻል እንደሚቻል ተገለጸ::

በኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራው ልዑክ በዞኑ የጪዳ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ እንቅሰቃሴዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ሰለሞን ሶካ የሚኒስተሩ ዋና ተግባር የወጣቶችን ስብዕና ግንባታ በማሳደግ የተለያዩ አጫጭር ሙያዊ ስልጠናዎችን ወስደው ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው የጪዳ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የጀመራቸውን ተግባራትን ማጠናከርና እንደመንግስትና ህዝብ ለዘርፉ መሻሻል ሁለ ዐቀፍ…

Read More

ኮርፖሬሽኑ አርሶ አደሩ የግብርና ግብዓት አቅርቦት እንዲያገኝ ለማስቻል ቅርንጫፍ ማዕከላትን እያጠናከረና እያስፋፋ ነው

የኢትዮጵያ ግብርና ስራዎች ኮርፖሬሽን አርሶ አደሩ የግብርና ግበዓቶችን በአቅራቢያው እንዲያገኝ ለማስቻል ቅርንጫፍ ማዕከላትን እያጠናከረና እያስፋፋ መሆኑን ገለጸ። የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ክፍሌ ወልደማሪያም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን በኮርፖሬሽኑ ቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓት ሜካናይዜሽን ማዕከል ግንባታና የበቆሎ ዘር ብዜት ማሳን በመስክ ተመልክተዋል። በዚህ ወቅት አቶ ክፍሌ እንዳሉት፤ ኮርፖሬሽኑ ግብርናውን ለማዘመንና ምርታማነትን ለማሳደግ…

Read More

የሱፐርቪዥን ስራዉ በአፈጻጸሙ ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማጎልበት፣ ድክመቶች ለማረም ለቀጣይ ስራዎች መሠረት የሚሆን ነው ፦አቶ ፀጋዬ ማሞ::

የሱፐርቪዥን ስራዉ በአፈጻጸሙ ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማጎልበት፣ድክመቶችን ለማረምና ለቀጣይ ስራዎች መሠረት እንደሚሆን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት አቶ ፀጋዬ ማሞ ገለጹ። የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በክልሉ በተለያዩ ዞኖች፣ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ላይ የፖለቲካ ና የአደረጃጀት ስራዎች የህዋሳትና መሠረታዊ ድርጅት ያሉበት ደረጃ በመፈተሽ የመስክ ምልከታ ያካተተ…

Read More