በክልሉ በሚገኙ ማዘጋጃ ቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ዘመናዊና ቀልጣፋ እንዲሆኑ ለማድረግና የተገልጋዩን ህብረተሰብ እርካታን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው ተባለ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ዲጂታል የማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ ስርአትን በሚዛን አማን ከተማ በይፋ አስጀምሯል። በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የክልሉ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ የመሬት ልማት ማናጅመንት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ጫናቸው ወንድሙ እንደገለጹት በክልሉ ከሚገኙ ብዘሀ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ዘመናዊ የማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ ለመዘርጋት…

Read More

ማሻ ከተማ የረዥም ጊዜ ጥያቄዎቿ እየተመለሷት ይሁን?

ማሻ ከተማ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ውስጥ ከሚገኙት ከስድስት ዞኖች አንዷ በሆነችው በሸካ ዞን ካሉት ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች አንዷ ናት። ማሻ በ1903 የተቆረቆረች እድሜ ጠገቧ ከተማ በርካታ የመንግስት አወቃቀሮችን ያሳለፈች ቅርብ ጊዜ የሸካ ዞን የዞኑን መቀመጫ ወደ ቴፒ ከተማ እስኪያዛዉር ድረስ የዞኑ ዋና ከተማ ሆና ሲታገለግል የነበረች ከተማ ነች። ማሻ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ…

Read More

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ‘አስተውሎት’ በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን ፊልም አስመረቀ::

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ‘አስተውሎት’ በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን ፊልም አስመርቋል ፡፡ ፊልሙ ትኩረቱን ኢንስቲትዩቱ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ባከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ የወደፊት የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ አድርጓል፡፡ ፊልሙን የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከሰውኛ ፕሮዳክሽን እና ኢንተርቴይንመንት ጋር በመሆን በጋራ አዘጋጅተውታል። በምርቃት ሥነ-ስርዓቱ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ…

Read More

በኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ የተመራ ልዑክ የበበቃ ኮፊስቴት የልማት ስራዎችን ጎበኘ::

ከኢፌዴሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከክልሉ ከዘርፉ ጋር ተያያዥነት ያላቸዉ መስሪያ ቤቶች እና የባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በቤንች ሸኮ ዞን የሚገኘውን የበበቃ ቡና ልማት፣ የቻንቹ ሙዝ ክላስተርን ጨምሮ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በሚድሮክ የኢንቨስትመንት ግሩፕ ስር በኢትዮ አግሪ-ሴፍት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ የበበቃ ኮፊስቴት ከ2 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚና ከ10 ሺህ በላይ ጊዜያዊ የሥራ ዕድል…

Read More

በዞኑ በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ተግባራት በሙሉ አቅም ተፈፃሚ ለማድረግ በቀሪ ወራት ሁሉ ዐቀፍ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።

የኮንታ ዞን አስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ ተካሂዷል። የአፈፃፀም ግምገማው በአስተዳደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና መሠረተ-ልማት ዘርፎች በመከፋፈል ነው የተገመገመው በአፈፃፀም ግምገማው ላይ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ነጋ አበራ የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች የተጣለባቸውን ተልዕኮ ለመወጣት ዕቅዳቸውንና አፈፃፀማቸውን እየፈተሹ ለውጤታማነት መትጋት እንደሚገባ አስረድተዋል። የህብረተሰቡን ሰላም፣ ፀጥታና ደህንነት ከማስጠበቅ ጀምሮ ፍትሃዊና…

Read More

የባታ ካሹ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ስራ 55 በመቶ መድረሱ ተገለጸ::

በሼይ ቤንች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ ታደሰ ኒሳብ የተመራው የሀይማኖት አባቶች፣ የቀበሌ ተወካዮች፣ የነጋዴ ማህብረሰቦች፣ የሞዴል አርሶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት ህንፃ እና የባታ ካሹ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ሂደትን ጉብኝት አድርገዋል። ድልድዩ በህብረተሰብ ተሳትፎ በ25 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር ወጪ እየተገነባ መሆኑን ያብራሩት የሼይ ቤንች ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ኒሳብ ስራው…

Read More

በሸገር ከተማ አስተዳደር በከባድ የማታለል ወንጀል ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግኝኙነትና ኮሚንኬሽን ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ በሸገር ከተማ አስተዳደር በመልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ በተለያዬ አራት ሀሰተኛ ስሞችን በመጠቀም በ15 ግለሰቦች ላይ በከባድ የማታለል ወንጀሎች በመፈፀም ክስ ተመስርቶበት በፖሊስ ሲፈለግ መቆየቱን ፖሊስ ኮሚሽኑ ገልጿል። የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ተጠርጣሪውን በተገኘበት እንዲያዝ ከፍርድ ቤት መያዣ ጋር በመላካቸው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ…

Read More

በህይወት ክህሎት እና በስብዕና ግንባታ ወጣቱ ላይ በመሥራት ሀገር ተረካቢ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባ ተገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች የህይወት ክህሎት ስልጠና ሰጥቷል ። የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ምክትል ና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ራሄል ሌዊ እንደገለፁት ከሀገራችን የህዝብ ብዛት ከፍተኛ ቁጥር የሚዘው ወጣቶች መሆናቸውን ጠቁመው 1.2 ሚሊዮን ወጣቶች…

Read More

የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት ሆነዋል – አቶ ቀጄላ መርዳሳ::

የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት ሊሆኑ በቅተዋል ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ቀጄላ መርዳሳ ተናገሩ። በሐረሪ ክልል የሸዋል ኢድ በዓል የመክፈቻ መርሃ-ግብር ተካሂዷል። በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ የሐረሪዎች የጥበብና የእውቀት ውጤቶች ድንበር ተሻግረው የዓለማችን ህዝቦች የቅርስ ሀብት መሆናቸውን ተናግረዋል። ሐረሪዎች ከደማቅ ታሪኮቻቸው ጎን ለጎንም የሰላምና የፍቅር…

Read More

የመስሪያ ቤቱን አደረጃጀት በማጠናከር ዓለም አቀፍ መስፈርትን ያሟላ የኦዲት ስራ ለማከናወን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ገለጸ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት የዋና ኦዲቴር መስሪያ ቤትየመስሪያ ቤቱን አደረጃጀት በማጠናከር ዓለም አቀፍ መስፈርትን ያሟላ የኦዲት ስራ ለማከናወን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር አቶ አቶ አስራት አበበ ገልፀዋል። ዋና ኦዲተሩ ይህንን የገለፁት ከፌዴራል ኦዲት መስሪያ ቤት በተሰጠ የስራ ግብረመልስ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተደረገ ዉይይት ነዉ።…

Read More