የቤንች ሸኮ ዞን የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና ተጠናቀቀ::

በሚዛን አማን ከተማ ስቴዲየም ለ11 ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው የቤንች ሸኮ ዞን የእግር ኳስ ክለቦች ሻምፒዮና በቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ ክለብ አሸናፊነት ተጠናቅቋል። በማጠቃለያው ላይ የተገኙት የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን ባስተላለፉት መልዕክት ስፖርት ለአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖሊትካዊ መስተጋብርን በማጠናከር ያለው ጠቀሜታ እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ አንስተው ይህንን የበለጠ ማጠናከር እና ማስቀጠል…

Read More

የአከባቢው ህዝብ ለእንግዳ የሚሰጠውን ክብርና እንክብካቤ በጎበኘነው ተፈጥሮ ሀብት ላይ አረጋግጠናል ሲሉ ልዑኳን ቡድኖች ተናገሩ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የሸካ ዞን ማሻ ከተማ ህዝብ እንኳን ለሰው ልጅ ለተፈጥሮ ሀብት የሰጠው እንክብካቤ የሚደነቅ መሆኑን በጎበኙት ተፈጥሮ ሀብት ማረጋገጣቸውን 3ኛው ክልል ዓቀፍ የባህል ስፖርቶችና ባህል ፌስቲቫል ውድድር ልዑካን ቡድኖች ተናግረዋል። 3ኛው ክልል ዓቀፍ 21ኛው የባህል ስፖርቶችና 17ኛው ባህል ፌስቲቫል ተወዳዳሪ ልዑኳን ቡድኖች ከውድድሩ ጎን ለጎን በሸካ ዞን ማሻ ወረዳ የሚገኘውን…

Read More

ዛሬ በሳዑዲ ጨረቃ ባለመታየቷ የዒድ-አልፈጥር በዓል የፊታችን ረቡዕ ይከበራል

ዛሬ በሳዑዲ ዓረቢያ አካባቢ ጨረቃ ባለመታየቷ የዒድ-አልፈጥር በዓል የፊታችን ረቡዕ እንደሚከበር መገለፁን ኤፍቢሲ ዘግቧል፡፡ ለተጨማሪ መረጃዎች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተላሉን በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/ ድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications በትዊተር twitter.com/sweprs በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi በቴሌግራም https://t.me/Debubmierabበዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication

Read More

ኢትዮጵያ እና ኔዘርላንድ በንግድ እና ኢንቨስትመንት ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለፁ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ዛሬ ከኔዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀንኬ ብርነስ ሰዋት ጋር ውይይት አድርገዋል። ውይይታቸው የሁለቱ አገራትን ግንኙነት እና ትብብር በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። አምባሳደር ታዬ በወቅቱ እንዳሉት የኔዘርላንድ መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር በልማት ትብብር፣ በኢንቨስትመንት እና በሰብአዊ ዕርዳታ ድጋፍ መስክ ያለውን ትብብር አድንቀዋል። ተጨማሪ ትብብሮችን ለማጎልበት በሚያስችሉ የኢኮኖሚ መስኮች አብሮ መስራት…

Read More

በመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የ1445ኛዉ የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም እንዲከበር የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታወቀ::

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽር ሰብስቤ ሻዎኖ እንደገለፁት በመላ የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በክልሉ ሁሉም ዞኖች፤ከተማ አስተዳደሮች እና ወረዳዎች በሰላም እንዲከበር የቅደመ ዝግጅት ስራዎችን በማጠናቀቅ ወደ ስራ መግባቱን ገልፀዋል፡፡ በዓሉን ተከትሎ ሊደርሱ ከሚችሉ የትራፊክ አደጋና ሊከሰቱና ሊፈጠሩ ከሚችሉ የእሳት ቃጠሎዎች ሁሉም ሰው እራሱንና ሌሎችን ሊጠብቅ እንደሚገባም…

Read More

‹‹በክልሉ ሁሉም አከባቢ ሠላምን በማረጋገጥ ለማህበራዊና ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ምቹ መደላድል መፈጠር ተችሏል››። አቶ አንድነት አሸናፊ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮና የተጠሪ ተቋማት የ9 ወራት የሴክተር ጉባኤ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። በጉባኤው ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊ ባለፋት 9 ወራት በክልሉ ሠላምን ለማረጋገጥ በቅንጅት በተሰራው ስራ አበረታች ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። አቶ አንድነት ህብረተሰብን በማሳተፍ የጸጥታ ተቋማት በቅንጅት በሰሩት ስራ…

Read More

የጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) የሩዋንዳ ጉብኝት ኢትዮጵያ ከሀገሪቱ ጋር ያላትን ግንኙነት የሚያጠናክር ነው: – ቢልለኔ ስዩም

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሩዋንዳ ጉብኝት ኢትዮጵያ ከሀገሪቱ ጋር ያላትን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ነው ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ቢልለኔ ስዩም ገለጹ፡፡ ቢልለኔ ስዩም የጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸውን የሩዋንዳ ኪጋሊ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በማብራሪያቸውም ፥ ጉብኝቱ በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን አንስተዋል፡፡ አንደኛው ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ፖል…

Read More

የዳውሮ ባህል፣ ታሪክና ቅርስ ለማልማት፣ ለማሳደግ እና ጠብቆ ለትውልድ ለማሻገር ህዝቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ ሰፋፊ ሥራዎች እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለፀ።

የዳውሮ ባህል፣ ታሪክና ቅርስ ለማልማት፣ ለማሳደግ እና ጠብቆ ለትውልድ ለማሻገር ህዝቡንና የልማት አጋሮችን በማሳተፍ ሰፋፊ ሥራዎች እየተሠራ እንደሚገኝ የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ ገልጸዋል። የብሄሩን ባህል፣ ታሪክና ምርምር ማዕከል ለማስገንባት ህዝባዊ ንቅናቄ እየተካሄደ እንደሚገኝና በሂደቱም ሰፊውን ህዝብ፣ የልማት አጋሮችን እና ወዳጆችን በማሳተፍ በተጀመረው የሀብት ማሰባሰብ እንቅስቃሴ በ 2 ወር ጊዜ ብቻ ከ10 ሚሊዮን…

Read More

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር ታካሂዳለች – አቶ ገብረመስቀል ጫላ

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር እንደምታካሂድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረ መስቀል ጫላ ገለፁ። አቶ ገብረ-መስቀል ጫላ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ከ20 ዓመታት በፊት የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እንቅስቃሴ ጀምራለች። ይሁንና በኮቪድ 19 ወረርሽኝና በሌሎች ምክንያቶች ድርድሩ ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን…

Read More

በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ የማድረጉን ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው

በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ ተደራሽ የማድረጉን ስራ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት አስታወቀ። የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮጀክትና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ዲጂታል መታወቂያ መስጠት መጀመሩን ከአንድ ወር በፊት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። ዲጂታል መታወቂያው በኢትዮጵያ ለሚገኙ ስደተኞች ማህበራዊ አገልግሎቶችን በተደራጀ…

Read More