በ18 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚገነባ የዛን አነስተኛ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት የመሠረተ ድንጋይ ተቀመጠ::
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው በቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ የዛን የድልድይ ግንባታ መሠረተ ድንጋይ አስቀመጥዋል። የድልድይ ግንባታዉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የገንዘብ ድጋፍ የሚሰራ ሲሆን የግንባታ አጠቃላይ ወጪ 18 ነጥብ 2 ሚሊየን የሚፈጅ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ ከጃንቹ ወደ ጃንቹታ በሚወስደው መንገድ ላይ…
