ኢትዮጵያና ፈረንሳይ የትብብር አድማሳቸውን በማስፋት የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮ-ፈረንሳይ የወዳጅነት ቡድን ዋና ሰብሳቢ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በፈረንሳይ ፓርላማ የአፍሪካ ቀንድ የወዳጅነት ቡድን ፕሬዝዳንት ሴናተር ሁግ ሳሪ ከተመራው የልዑካን ቡድን ጋር ተወያይተዋል። ውይይቱ የሁለቱ ሀገራት የወዳጅነት ቡድን አባላት በፓርላማ ዲፕሎማሲ፣ በሕዝብ-ለሕዝብ ዲፕሎማሲና የምርጫ ስርዓትና አፈጻጸምን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ማጠናከር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ…
