




አገልግሎቱን ለማስፋት ታልሞ በተከናወነ ስራ በዞኖች አካባቢ የተጀመሩ የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ተቋማት ግንባታ ሂደታቸው በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መሶብ አንድ ማዕከልአገልግሎት ምክትል ስራ አስፈፃሚ አቶ አህመዲን አወል እንደገለጹት በክልሉ የመጀመሪያ የሆነው የሚዛን-አማን ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለሕብረተሰቡ ሰፊ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በማዕከሉ አምስት የክልልና አራት የፌዴራል ተቋማት 35 የተለያዩ አገልግሎቶች እየተሰጡ እንዳሉ የገለጹት አቶ አህመዲን ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ ከ24 ሺህ በላይ ዜጎች አገልግሎት መስጠቱን ተናግረዋል።
በክልሉ መሶብ አንድ ማዕከል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ጊዜ ወዲህ 20 ሺህ 129 ተገልጋዮች ቀርበው ዲጂታል አገልግሎት ያገኙ ሲሆን 3 ሺህ 958 በላይ ተገልጋዮች ደግሞ መንቀሳቀስ ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን መገልገል መቻላቸው ተገልጿል።
ማዕከሉ በተቀመጠ ስታንዳርድ መሠረት ከእጅ ንክኪ ነፃ ዲጂታል አገልግሎት እየሰጠ በመሆኑ ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረ የህዝብ ቅሬታ መፍታት እያስቻለ መሆኑን አቶ አህመድን ተናግረዋል።
ማዕከሉ ለዜጎች በሚሰጠው አገልግሎት ከተገልጋዮች ኦንላየን በሰበሰበው የተገልጋይ እርካታ መሠረት 97 ነጥብ 6 በመቶ ለማድረስ የተቻለ ሲሆን በቀጣይ የተገልጋይ እርካታን መቶ በመቶ ለማረጋገጥ እየተሰራ እንዳለም አቶ አህመዲን ገልጸዋል ሲል የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ ዘግቧል።
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መጀመር በመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ከሕብረተሰቡ ሲነሳ የነበረውን እንግልት፤ ጉልበትና የሀብት ብክነት በሰፊው እየቀረፈ እንደሚገኝ ምክትል ስራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።
