
የኑሮ ውድነትን በዘላቂነት መቅረፍ የምንችለው ምርታማነትን በመጨመር ነው፡፡ የንግድ ስርዓቱን ማዘምንም ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የኑሮ ውድነቱ እጅ አጠር ዜጎች ላይ ጫና እንዳይፈጥር መንግስት ከ300 እስከ 400 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት መድቧል፡፡ ማዕድ ማጋራት፣ ትምህርት ቤት ምገባ እና እሁድ ገበያ መንግስት አቅመ ደካሞችን ለማገዝ የሚያደርገው ጥረት አካል ነው፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም 249 ሺህ አቅመ ደካማ ዜጎች መኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ይህ መንግስት ባለሃብቶችን በማስተባበር ያከናወነው ስራ ነው፡፡ የዋጋ ንረቱ አሁን ላይ ወደ 17 በመቶ ዝቅ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፤ ይህን ወደ ነጠላ አሃዝ ማውረድ የመንግስት ቀዳሚ ትኩረት ነው፡፡
