የፌደራል ሱፐርቪዥን ቡድን በክልሉ በቤንች ሸኮ ዞን በደቡብ ቤንች ወረዳ እየተሰሩ ያሉትን የልማት ስራዎችን ጎበኘ ።

Spread the love

በፕላንና በልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር በዶ/ር ፍጹም አሰፋ የተመራ የፌደራል ሱፐርቪዥን ቡድን በቤንች ሸኮ ዞን በደቡብ ቤንች ወረዳ ግብርና ልማት ስራ ጃንቹ የመዝ ክላስተር እርሸ፣ በቅርቡ በጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አቢይ አህመድ መሠረተ ድንጋይ ተቀምጦ ወደስራ የተገበውን የደንቢ ገበታ ለትውልድ የፕሮጀክት አፈፃፀም ያለበት ደረጃ እና በሌማት ትሩፋት ውጤቶችአንዱ አካል የሆነው የማር ምርት ተመልክቷል።

በደቡብ ቤንች በ200 አርሶአደሮች በራስ ተነሳሽነት እየለማ ያለው 85 ሺህ ሄክታር ማሣ ጃንቹ የመዝ ክላስተር የሙዝ እርሻ፣ በወረዳው የተለያዩ የፍራፍሬ፣ የበቆሎ ፣ የሽንኩርት እንዲሁም የሚዛን አማን አዳሪ ትምህርት ቤትን ተዘዋውረው ተመልክቷል።

በተከተል ወ/ሚካኤል

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *