የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግስት ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል ፡፡

Spread the love

የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ በጉባዔዉ መክፈቻ ባደረጉት ንግግር ምክርቤቱ ባለፉት 6 ወራት በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ኃላፊነት ለመወጣት የተለያዩ ጥረቶች ማድረጉን ተናግረዋል ፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ከፍተኛ የህግ አውጭ አካል በመሆኑ የፌዴራሉን ህገ መንግስት በማይጻጸር መልኩ በክልሉ ውስጥ ተፈጻሚ የሚሆኑ ህጎችን የማውጣት፣የአስፈጻሚ አካላትን ተግባር የመከታተልና የመቆጣጠር ስራዎችን ሲከናውን መቆየቱን አፈ ጉባኤ ወንድሙ ተናግረዋል ፡፡

ምክር ቤቱ በ6 ወራት ውስጥ የተለያዩ ስራዎችን ማከናወን መቻሉን የገለጹት ዋና አፈ ጉባኤው በኦዲት ስራዎች ላይ በኦዲት ግብረ ሀይል ስራዎችን በመገምገምና አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ መቻሉን ተናግረዋል ፡፡

በጉባኤው የ6ኛ ዙር 3ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ ረቂቅ ቃለ ጉባኤን መርምሮ ማጽደቅ፣የአስፈጻሚ አካላት የ2017 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት መርምሮ ማጽደቅ፣ከተቋማት የቀረቡ አዋጅና ደንድ መርምሮ ማጽደቅ፣የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔት ዎርክ የ2017 በጀት ዓመት የ6ወራት የስራ ዕቅድ መርምሮ ማጽደቅ እና ልዩ ልዩ ሹመቶችን መርምሮ ማጽደቅ የጉባኤው አጀንዳ እንደሆኑም ታውቋል ፡፡

በታጠቅ አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *