




በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በብልጽግና እሳቤዎች ቅኝት በርካታ ተግባራት በስኬት ማከናወን እንደተቻለ የቦንጋ ብዝሃ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት ሰብሳቢ አቶ በላይ ኮጁአብ ገለጹ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የብልጽግና ፓርቲ የቦንጋ ብዝኃ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት የ2017ዓ.ም የአባላት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው
የቦንጋ ብዝሃ ማዕከል የኢኮኖሚ ዘርፍ ብልጽግና ህብረት ሰብሳቢ አቶ በላይ ኮጁአብ በማጠቃለያ ኮንፈረንሱ እንደገለጹት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህብረቱን ተቋማዊ አደረጃጀቶችን በማጠናከር ፈርጀ ብዙ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
አመራሩና አባሉ በተሰማራበት መስክ ሁሉ አገልጋይ ተኮር እሳቤን በመላበስ ለብልጽግና ጉዞ ስኬት መሰረት የሚጥል ውጤት ተመዝግበዋል።
በፓርቲው አደረጃጀትና አሰራር መሠረት የብልጽግና ቤተሰብና ህብረት ተልዕኮውን በብቃት መፈጸም እንዲችሉ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የገለጹት አቶ በላይ የአባሉቱ የፖለቲካ አስተሳሰብ ጥራት ከጊዜ ወደ ጊዜ አየተጠናከረ መምጣቱን ገልጰዋል።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ልዩ ረዳት አቶ አለማየሁ አይበራ ፓርቲያችን ብልጽግና በመደመር መንገድ የህዝቡን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ በርካታ ስኬቶችን አስመዝግቧል ተብለዋል።
ፓርቲያችን ያነገባቸውን ህልሞችን ወደ ሚጨበጥ ውጤቶች ተመዝግበዋል።
የፓርቲና የመንግስት ኢኒሼቲቦች በበጋ ስንዴ ልማት፣ በአረንጓዴ አሻራ ፣ በሌማት ትሩፋት ፣በቡና ልማት፣ በሰው ተኮር አሳቤዎች እንዲሁም በሌሎች መስኮች አበረታች ውጤቶች ሊመዘገብ የቻለው አመራሩን፣ አባሉንና የፓርቲው እሳቤዎችን በላቀ ብቃት መተግበር መቻላቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል።
አመራሩና አባሉ እስካሁን የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ በማስቀጠል የጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ በልዩ ቁርጠኝነት መትጋት ይጠበቃል ብለዋል።
ልማትን የሚያደናቅፉ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን አባሉ አምሮ መታገል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
የ2017 ዓም የብልጽግና የህብረት አፈጻጸምና የ2018 ዓም ዕቅድ ቀርበው ውይይት እየተደረገ ይገኛል ሲል የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዘግቧል።
