የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔዉን ሊያካሄድ ነዉ

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ከሐምሌ 14_16/2017 ዓ.ም ድረስ በታርጫ ከተማ እንደሚካሄድ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ገልጸዋል።

ከጉባኤው ጋር በተያያዘ ለሚዲያችን መግለጫ የሰጡ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ለጉባኤው ስኬታማነት አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።

በጉባኤ የ2017 በጀት አመት የአስፈጻሚ አካላት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትና ሌሎች አጀንዳዎች ቀርቦ ወይይት እንደሚደረግም አንስተዋል።

የምክር ቤቱ አባላትና ተጋባዥ እንግዶች ከሐምሌ 13/2017 ጀምሮ ወደ ታርጫ ከተማ እንደሚገቡ የገለፁ ዋና አፌ ጉባኤ ጉባኤው በስኬት እንዲጠናቀቅ የባለድርሻ አካላት ሀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *