ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረች

Spread the love

በኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ተችሏል አለ የጤና ሚኒስቴር፡፡

የኢትዮጵያ ድንገተኛ የማሕበረሰብ ጤና አደጋ ፈጣን ምላሽና አመራር ስኬቶች እንዲሁም የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ቁጥጥር ማብሰሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

በመርሐ ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ አጋር አካላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም ሚኒስቴሩ አክሞ ማዳን እና መከላከልን መሰረት በማድረግ የዜጎችን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ለወረርሽኝ የማይበገር ጠንካራ የጤና ሥርዓት ለመገንባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

በዚህ መሰረትም በቅርቡ በኢትዮጵያ ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉ ተገልጿል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *