



የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው ጉብኝቱ የቅርሱ መጠበቅን ባሕላዊ እና አለም አቀፍ ዋጋ ያመላከተ ነበር።
እ.ኤ.አ በ2019 ከተከሰተው የእሳት አደጋ በኋላ የተደረጉ የጥበቃ ሥራዎች ፈረንሳይ ለታሪካዊ ምልክቶቿ ጠብቃ ለመጪ ትውልዶች ለማቆየት ያላትን ፅኑ አቋም የሚያሳዩ ናቸው ሲልም ገልጿል።
ጉብኝቱ ለኢትዮጵያ ትርጉም ያለው ትምሕርት የሰጠ መሆኑን ጠቁሞ ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እስከ ጎንደር ፋሲለደስ እስከ አባጅፋር ጅማ ቤተመንግሥት እና በርካታ ቅርሶች ድረስ አቻ የማይገኝለት የታሪክ እና የባሕል ሀብት እንዳላት ሀገር ኢትዮጵያ ሀገራችን የቅርስ ጥበቃ እና እድሳትን ቅድሚያ የምትሰጥበት በርካታ ፀጋ አላትም ነው ያለው።
ቱሪዝምን ማስፋፋት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቁልፍ የትኩረት መስክ በመሆን በኢኮኖሚ ሪፎርም አጀንዳ ከአምስቱ ምሰሶዎች አንዱ ሆኖ እየተሰራበት ይገኛል ሲልም ገልጿል።
ከአለም አቀፍ ምርጥ ተመክሮ በመማር ኢትዮጵያ የባሕል ሀብት ቅርሶቿን የመጠበቅ እና ቀጣይነት ያለው የቱሪዝም ልማት ሥራ ጥረቷን ለማጠናከር ትችላለችም ነው ያለው በመልዕክቱ ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
