



ርዕሰ መስተዳድሩ ባቀረቡት ሪፖርት በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ የተከናወኑ ሥራዎች ው ጤታማ መሆናቸውን አብራርርዋል ፡፡በዚህም ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፡-
በዋና ዋና የአዝርዕት ሰብሎች በመኸር፣ በበጋ መስኖ እና በበልግ ወቅት 745,090.5 ሄ/ር ማሳ በዘር ተሸፍኗል፡፡
በበጀት ዓመቱ 20 ሚሊየን 632 ሺህ 359 ኩንታል ምርት ተሰብስቧል፡፡
በበጋ መስኖ ስንዴ 5,017 ሄ/ር መሬት በዘር በመሸፈን 149 ሺህ106 ኩንታል ምርት ተገኝቷል፡፡
የኩታ ገጠም እርሻን ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ 167 ሺህ 426 ሄክታር መፈጸም ተችሏል፡፡
በሆርቲካልቸር ሰብሎች በአትክልት፣ሥራሥር፣ እንሰትና ፍራፍሬ በበልግ መስኖና መኸር አዝመራ 326 ሺህ 698 ሄክታር ለምቷል ፡፡
ከምርት አንጻርም 66 ሚሊን 958 ሺህ 777 ኩንታል ምርት ተገኝቷል።
የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት አኳያ 132,000 ኩንታል ታቅዶ 156,085 ኩንታል ማቅረብ ተችሏል ፡፡
የምርጥ ዘር አቅርቦትን በተመለከተም 80 ሺህ 064 ኩንታል ለማቅረብ ታቅዶ 82 ሺህ 507 ኩንታል ቀርቦ ተሰራጭቷል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ ተግባር አፈጻጸም በግብርና መዋቅር ብቻ በክረምት የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው 145,628,040 ችግኞች በመትከል 44‚553 ሄክታር መሬት ተሸፍኗል፡፡
የሌማት ትሩፋትን ውጤታማ ለማድረግ አኳያ በወተት 186 ፤በዶሮ 148 ፤ በንብ 327 ፤በዓሳ 14 እንዲሁም በቀይ ስጋ 167 መንደሮችን በማደራጀት እየተሰራ ነው ፡፡
የእንስሳትን ምርትና ምርታማነት ለማሻሻል እንስሳት ዝርያን ለማሻሻል 56,726 ላሞችንና ጊደሮችን ማዳቀል ተችሏል።
በሁሉም እርባታ ደረጃዎች 357 ሚሊዮን ሊትር ወተት ማምረት ተችሏል።
የቡና ማሳ ሽፋንን ከማሳደግ አንጻር በበጀት ዓመቱ 88,546,348 የቡና ችግኝ በማዘጋጀት 87,944,188 ቡና ተተክሏል፡፡
ከቅመማ ቅመምና ሻይ ልማት ሥራዎች አፈፃፀም አንጻር ከነባር ለምርት ከደረሰ 75,064 ሄ/ር ማሳ ላይ 385,465.4 ቶን ምርት ተሰብስቧል፡፡
በበጀት ዓመቱ በቡና የታጠበና ያልታጠበ 48 ሺህ 153 ቶን ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ ቀርቧል፡፡
የተለያዩ ችግኞችን በመትከል ክልላዊ የደን ሽፋን ከነበረበት ከ42.9% ወደ 43.8% ማድረስ ተችሏል፡፡
የነዳጅ ግብይት ስርዓት በኤሌክትሮኒክስ ግብይት አገልግሎት በሚሰጡ 33 የነዳጅ ማደያዎች 57,212,202 ሊትር ናፍጣ እና 9,208,740 ሊትር ቤንዚን ቀርቦ ተሰራጭቷል፡፡
በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 252 የንግድ ድርጅቶች እርምጃ ተወስዶባቸዋል ።
በህገ-ወጥና በኮንትሮባንድ የንግድ እንቅስቃሴ 48,405,538 ብር የሚገመት ምርት ተይዞ ለመንግስት ገቢ ተደርጓል፡፡
ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በግብርና 67 ፤ በኢንድስትሪ 25 እና በአገልግሎት ዘርፍ 22 አዲስ ፍቃድ መስጠት ተችሏል፡፡
በበጀት ዓመቱ 89 አነስተኛና መካከለኛ አዳዲስ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎችን ወደ ዘርፉ እንዲቀላቀሉ ተደርጓል፡፡
ከስራ ዕድል ፈጠራ አንጻር በቋሚ እና በጊዜያዊ 140,894 ዜጎች የስራ ዕድል በበጀት ዓመቱ የስራ ዕድል ተፈጥሯል ፡፡
በበጀት ዓመቱ ጠቅላላ ገቢ ብር 10 ነጥብ 07 ቢሊየን ለመሰብሰብ ታቅዶ ብር 9 ነጥብ 66 ቢሊየን (96%) መሰብሰብ ተችሏል፡፡
የክልላዊ ሀብት ግመታ ጥናት ማስጀመሪያ ምዕራፍ ስራዎችን ተጠናቀዋል።
በታጠቅ አበበ
