ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እየቀረቡ ካሉ ጥያቄዎች መካከል

Spread the love

👉 በአንዳንድ የአማራና የኦሮሚያ ክልል የሚስተዋሉ ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ምን ተሰርቷል?

👉 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ እንዲሆንና በጸጥታ ችግሮች ምክንያት እንዳይስተጓጎል በመንግሥት በኩል እየተሰሩ ያሉ ጉዳዮች ላይ ምንድናቸው ?

👉ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ውጤታማ እንዲሆንና የቀጣይ የሀገሪቱ መጻሂ እድል ብሩህ እንዲሆን ከማን ምን ይጠበቃል?

👉 በተለያዬ ጊዜ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስና ዘላቂ ሰላም ለማስፈን ምን እየተሰራ ነው?

👉 ህወሐት ለዓመታት ሲያደርግ እንደኖረው የተፈናቀሉ ዜጎችን ለፖለቲካ እየተጠቀመ ድጋፍ እንዳይደረግና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዳይመለሱ እያደረገ ይገኛል።

ይህንን ሁኔታ ለመፍታት በመንግሥት በኩል ምን እየተሰራ ይገኛል?

👉 በትግራይ ክልል የህውሃት ክፋይ በሆነው የአዛውንቶች ቡድን ምክንያት በክልል ስርዓት አልበኝነትና የግጭት ድባብ ዳግም እንዲያንዣብብ፣ የትግራይ ህዝብም በውስብስብ ችግር ውስጥ ይገኛል፡፡ የትግራይ ክልል አሁናዊ የሰላም ሁኔታ ምን ላይ ይገኛል?

👉 የትግራይ ክልል በሃገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረውና 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማድረግ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር እየተሰሩ ያሉ ስራዎችች ምንድናቸው?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *