የኮንታ ዞን ም/ቤት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነዉ

Spread the love

‎የኮንታ ዞን ም/ቤት 4ኛ ዙር 4ኛ የስራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባኤ ማካሄድ ጀምሯል።

‎ጉባኤው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 2 ቀናት የሚቆይ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

‎በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ም/ቤት አፈ- ጉባኤ የተከበሩ አቶ ብርሃኑ አቱሞ ም/ቤቶች በህገ መንግስቱ የተሰጣቸውን የህብረተሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዕድገት እንዲፋጠን የማድረግ ኃላፊነት በመሆኑ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

‎ባለፉት 6 ወራትም የወጡ ህጎች አፈፃፀማቸውን መከታተል የመገምገምና ግብረ መልስ የመስጠት፣ የዜጎች መብቶችና ነፃነት እንዲከበርና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን የማድረግ፣ የህዝብ አስተያየት መድረክ በማዘጋጀትና አቤቱታና ጥቆማ በመቀበል መፍትሄ እንዲሰጥ የማድረግ ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።

‎በዞኑ በጋራ ጥረት በርካታ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት መብቃታቸው የህብረተሰቡን እርካታ ከፍ እያደረጉ ናቸው ያሉት አቶ ብርሃኑ በቀጣይም መሻሻሎች በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ የተሻለ ውጤት እንዲመዘገብ መስራት ያሻል ብለዋል።

‎አክለውም ዘንድሮ የሚካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የም/ቤቱ አባላት የጎላ ሚናቸውን እንዲወጡና ለምርጫ እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርበዋል።

‎በጉባኤው የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የአስፈጻሚ አካላት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ የተለያዩ ደንቦች፣ የከፍተኛ ፍ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት፣ ልዩ ልዩ ሹመቶችና ሌሎች አጀንዳዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው እንደሚፀድቁ የኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዘግቧል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *