



ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው ይሄው መደበኛ ጉባኤ ያለፈውን 4ኛ ዙር 11ኛ ዓመት 23ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃሌጉባኤ መርምሮ በሙሉ ድምጽ በማጽደቅ ስብሰባውን ጀምሯል::
የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ በሚኖረው የ2 ቀናት ቆይታ የተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ የሚወያይ ሲሆን ከነዚህም መካከል የካፋ ዞን የአስፈፃሚዎች የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ: የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት አፈፃፀም ሪፖርት ማድመጥ እንድሁም አዳዲስ የቀበሌ መዋቅሮችን ውሣኔ ማስተላለፍና ልዩ ልዩ አጀንዳዎች ቀርቦ በመወያየት ውሳኔ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል::
የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ እንዳሻው ከበዴ የአስፈፃሚዎች የ2017 ዓ/ም የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እያቀረቡ ናቸው::
ጉባኤው ለ2 ተከታታይ ቀናት የሚቀጥል መሆኑን
የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
