በበጀት ዓመት ከ30ሺህ ለሚበልጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች አግልግሎት መስጠቱን የቴፒ ከተማ የህዝብ መድኃኒት ቤት አስታወቀ።

Spread the love

በህዝብና በከተማ አስተዳደሩ ትብብር በ2015 ተቋቁሞ ወደ አግልግሎት የገባው የቴፒ ከተማ የህዝብ መድኃኒት ቤት፤ በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት ከ30ሺህ ለሚበልጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች አግልግሎት መስጠቱ የመድኃኒት ቤቱ ስራ-አስኪያጅ ወ/ሮ ተስፋነሽ ደስኖ ገልጸዋል።

የመድኃኒት ቤቱ መቋቋም በመንግስት የጤና ተቋማት የማይገኙ መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ በቀላልና ተመጣጣኝ ዋጋ ገዝቶ መጠቀም እንዲችል ምቹ ሁኔታን የፈጠሩ መሆኑን ነው ስራ-አስኪያጇ የጠቆሙት።

ወ/ሮ ተስፋነሽ አክለው፥ በተመጣጣኝ ዋጋ ለፔፒና የአከባቢው ማኅበረሰብ ክፍሎች አግልግሎት ለመስጠት አላማ ይዞ የተቋቋመው የህዝብ መድኃኒት ቤቱ የአግልግሎት አሰጣጡን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻሻለ ይገኛል።

ከኅብረተሰቡ የሚነሳውን የመድኃኒት ፍላጎትና አቅርቦት ያለመጣጣም ችግር ለመቅረፍ የመድኃኒት መዝርዝርና ልየታን መሠረት ያደረገ ግዥ ለመፈጸም ከአቅራቢዎች ጋር አስቀድሞ ውል እንደሚገባ ተናግረዋል።

በመድኃኒት ቤቱ አግልግሎት ስያገኙ ከነበሩት ተገልጋዮች መካከል ያነጋገርናቸው እንደገለጹት፥ ተቋሙ ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ ህጋዊ መድኃኒቶችን ለኅብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ እንደሆነ በማንሳት ቀጣይ የአግልግሎት አድማሱን እንዲያሰፋም ጠይቀዋል።

የቴፒ ከተማ የህዝብ መድኃኒት ቤት የቦርድ ሰብሳቢ የከተማው ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ በበኩላቸው ቀጣይ የአግልግሎት ማዕከል በመጨመር ተደራሽነትን ለማስፋት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ካንቲባው አክለው ከዚህ ቀደም በህብረተሰቡ ዘንድ በመድሃኒት አቅርቦት ችግር የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ሲያነሳ መቆየቱን አስታውሰው፥ የመድኃኒት ቤቱ መቋቋም ችግሮቹን በዘላቂነት ከመፍታት አኳያ አውንታዊ ውጤት እያመጣ ነው ብለዋል።

መድኃኒት ቤቱ አሁን ላይ የራሱን ካፒታል በመያዝ በተሻለ መልኩ የተለያየ መድኃኒቶችን ለኅብረተሰቡ እያቀረበ እንደሚገኝ የገለጹት ካንቲባ ወንድሙ የከተማው መንግሥት አግልግሎቱ አሁን ካለበት ደረጃ ለማሻሻል የበጀት ድጎማ እንደሚያደርግም ተናግረዋል።

በከተማው አሁን ላይ ያለውን አንድ ብቻ የማህበረሰብ መድኃኒት ቤት በቀጣይ በሌሎች የከተማው ቀበሌያት በማስፋት የአከባቢውን ህብረተሰብ የመድኃኒት አቅርቦት ጥያቄ ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራም ነው ካንቲባው የጠቆሙት።

በዕድገቱ በዛብህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *