


በታርጫ ከተማ ከሐምሌ 15 እስከ 16/2016 ዓ.ም ድረስ ስካሄድ የቆየው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር፣3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 6ኛ መደበኛ ጉባኤው የተለያዩ ሹመቶችን በማጽደቅ ተጠናቋል።
በዚህም መሠረት:- በምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ ውስጥ
1. ክብርት ወ/ሮ አምሳሌ ንጋቱ:- የህግ ፍትህና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ሆነው ተሾመዋል።
2. ክብርት ወ/ሮ ገነት ታፈሰ:- የበጀት ፋይናንስና ኦዲት ጉዳዮፐች ቋሚ ኮሚቴ አባል
3. የተከበሩ አቶ ንጉስ ወ/ጊዮርጊስ:- የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል በመሆን ተሹመዋል።
ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለመሀል ፈጽመዋል።
በዕድገቱ በዛብህ
