




ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ) በተገኙበት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግሥት ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የደረጃ ‘ሐ’፣’ለ’ እና ‘ሀ’ ግብር ከፋዮች የግብር ማስጀመሪያ ክልላዊ ንቅናቄ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ
በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ክልላዊ የንቅናቄ መድረኩ ”ለክልላችን ልማት ግብርን በታማኝነት በሚል መርሕ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘዉ።
በመድረኩ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣የክልሉ አስፈጻሚ አካላት፣የክልሉ የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ህይወት አሰግድን ጨምሮ ከክልል እስከወረዳ ድረስ ያሉ ከፍተኛ አመራሮችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ናቸው ።
በፍቅር ከበደ
