


ፕሮጀክት በባህሪው እሳት ዳር እንደተቀመጠ ህፃን ነው፤ በየጊዜው ትኩረት እና ክትትል ይፈልጋል፣
የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ ውስንነት አለ፣ ፕሮጀክቶችን እኔ የመንግስት ቅጥረኛ ነኝ፣ ኮንትራክተር ነኝ ከማለት ወጥቶ ቤቴን ነው የምሰራው ብሎ በማስብ ፕሮጀክቶችን አሳምሮ የመስራት ውስንነት አለ፣
መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ የመጨረስ ችግር የለበትም፤ ነገር ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የፕሮጀክት ፍላጎቶች እና የመንግስት የማስፈፀም አቅም ላይ ችግር አለ፣
ኢትዮጵያ ውስጥ 346 የመንገድ ፕሮጀክቶች አሉ፣ 1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ወጭ የሚጠይቅ ከ26 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ፕሮጀክት እየተሰራ ነው፣
የመብራት ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ፣ በመብራት ብቻ የ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላርፕሮጄክት አለን፣ የ5 ቢሊየን ዩሮ ፕሮጄክት አለን፣ የ110 ቢሊየን ብር ፕሮጄክት አለን፡፡
በተጨማሪም የፌዴራል መንግስት ከ200 ቢሊየን ብር በላይ በጀት በመመደብ አነስተኛ እና መካከለኛ ግድቦችን እየገነባ ነው፡፡
