የክልሉ ምክር ቤት ጉባዔ ከጥር 30/2016 ጀምሮ ሊካሄድ ነዉ::

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ምክርቤት 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባዔ ከፊታችን ጥር 30/2016 እስከ የካቲት 1/2016 ዓ/ም በታርጫ ከተማ እንደሚካሄድ አስታወቀ።

ጉባኤውን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የክልሉ ምክርቤት ዋና አፈ ጉባዔ የተከበሩ አቶ ወንድሙ ኩርታ ለጉባኤው አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል ።

በዚህም ለጉባኤው ተሳታፊዎች ጥሪ መተላለፉን አፈጉባዔ ወንድሙ ኩርታ አስረድተዋል ።

በጉባኤ የአስፈጻሚ ተቋማት የ2016 በጀት ዓመትየ6 ወር የስራ አፈጻጸም ቀርቦ በጉባኤው አባላት እንደሚገመገም ጠቅሰዋል ።

በጉባኤው የተለያዩ ረቂቅ አዋጆች እና ሌሎች አጀንዳዎች ቀርበው እንደሚጸድቁ አፈጉባኤ ወንድሙ ኩርታ ገልጸዋል።

በታጠቅ አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *