ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ነው

Spread the love

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ዛሬ በኢትዮጵያ በተለያዩ ከተሞች እየተከበረ ይገኛል።

ዘንድሮ ቀኑ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ49ኛ ጊዜ “ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል” በሚል መሪ ሀሳብ ይከበራል።

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ ከተማ አስተዳድሮች በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ እንደሚገኝ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *