“ከቃል እስከ ባህል ” በብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የውሳኔ አቅጣጫዎች ላይ የብልጽግና ወጣቶች ክንፍ ሚና በሚል መሪ ሀሳብ ከወጣቶች ጋር ውይይት በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ጀምሯል።

Spread the love

በዚሁ ዞናዊ የወጣቶች ክንፍ የውይይት መድረክ ከ400 በላይ ወጣቶች ተሣታፊ እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል።

በመድረኩ የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አጥናፉ ኃይሌን ጨምሮ የዞን እና የቦንጋ ከተማ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የብልጽግና ወጣቶች ክንፍ ሥራ አስፈፃሚ አባላት እንድሁም ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እየተሳተፉ ናቸው::

ተሣታፊ ወጣቶች ዜጎች በደም እጦት እንዳይሞቱ በሚል እሳቤ ፓርቲው ትኩረት ሰጥቶ ከሚተገብራቸው በጎ ሥራዎች አንዱ የሆነውን የደም ልገሣ ፕሮግራም ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቆ ለመለገስ በመጠባበቅ ላይ ናቸው::

በመድረኩ ሰነድ ቀርቦ መወያየትን ጨምሮ የተለያዩ መርሃ ግብሮች የሚከናወኑ ሲሆን የወጣቶች ክንፍ የውይይት መድረክ በተዋረድ እስከ ወረዳና ቀበሌ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ታውቋል ሲል የዘገበው የካፋ ዞን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *