በኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካ ፍላጎትን የማሳኪያ ስልት ልምምድ ሰላምን እየፈተነ ነው፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Spread the love

ባለፉት 50 እና 60 ዓመታት ሃሳብ ይዞ በሃሳብ አሸንፎ ስልጣን የመያዝ ልምምዱ ያልታየ በመሆኑ እንደባህልም እየተወሰደ ያለው የፖለቲካ ፍላጎትን በጠብመንጃ የማሳካት ፍላጎት አንዱ አደገኛ ስብራት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የሰላም ችግር መሰረቱ የፖለቲካ ፍላጎት ማሳኪያ መንገድ ላይ ያለው ልምምድ መሆኑን ተናግረዋል።

የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥም ቢሆን እንደሀገር ያለን ልምምድ በውይይት ወይም በሽምግልና ለመፍታት ያለው ልምምድ አንስተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

በእነዚህ ችግሮች ውስጥም ተሁኖ የሰላም ጅማሮዎች ሲኖሩ ደግሞ ከግራም ከቀኝም በሰላም መንገድ ላይ ወጥመድ ማስቀመጥ መኖሩ የሰላም ልምምዱ ወደ ኋላ እንዲመለስ የማድረግ ልምምዱም ከፍተኛ ነው ብለዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *