







የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው፤ በዳውሮ ዞን የተደራጁ ወጣቶችና ሴቶች በበጋ መስኖ ተግባር በከፍተኛ ሁኔታ እየተሳተፉ እንደሚገኙ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
በዳውሮ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች አትክልት፣ስራስርና ፍራፍሬ በማልማት ተጠቃሚነታቸው እየተረጋገጠ የመጡ የተደራጁ ወጣቶች አትክልትና ፍራፍሬ ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የአከባቢውን ፀጋ ወደ ሃብት በመለወጥ የሚያኮራ ተግባር በመፈፀም ላይ ይገኛሉ ብለዋል አቶ ማስረሻ በላቸው።
