በግብርናው ዘርፍ መሰረታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል ፡፡

Spread the love

ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ

ርዕሰ መስተዳድሩ ባቀረቡት የአፈጻጸም ሪፖርት

በመኸር እና በበልግ በዋና ዋና የአዝርዕት ሰብሎች 688 ሺ ሄክታር መሬት በዘር ተሸፍኗል ፡፡

➣ 19 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መሰብሰብ ተችሏል፡፡

➣ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦትና ሥርጭት አኳያ 190,013 ኩ/ል ተሰራጭቷል ፡፡

➣ በተቀናጀ ተፋሰስ ልማት 1,073 ንዑስ ተፋሰስ ወይም 217,384 ሄ/ር ማልማት ተችሏል ፡

➣ በአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ በክረምት የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው 129,102,135 ተተክለዋል ፡፡

➣ የአንድ ጀንበር ተከላ 20,512,583 ችግኞች ተተክለዋል ፡፡

➣ 54 ሺ 795 ሜትሪክ ቶን የታጠበና ያልታጠበብ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብም ተችሏል

➣ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ለማሻሻል በብሔራዊ የገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ስርዓት 122,469 ማሳዎች በ8 ወረዳዎች በ141 ቀበሌዎች ገብተዋል ፡፡

➣ 1,915,110 የአንድ ቀን ጫጩት እና 2.7 ሚሊየን ቀብና ኮክኔ ማሰራጨት ተችሏል ፡፡

➣ 92,632 የተለያዩ ቀፎዎችን በማሰራጨት 70,434 ቶን የማር ምርት ማምረት ተችሏል፡፡

➣ የሌማት ትሩፋት ስራዎች ውጤታማ ከማድረግ አኳያ 266 የወተት መንደሮች ፤447 የዶሮ መንደሮች 977 የንብ ሀብት መንደሮች 73 የዓሳ ግብርና ፣መንደሮች ተደራጅተዋል ፡፡

➣ 52,276.6 ቶን የቅመማ ቅመም ምርት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ ተችሏል ፡፡

➣ 6,654 ቶን የሻይ ምርት ለገበያ ማቅረብ ተችሏል፡፡

➣ ከአፈር ማዳበርያ ዕዳ አመላለስ ጋር በተያያዘ ከ2014/15 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 2016/17 በጀት ዓመት ብር 1,112,969,054.96 ዕዳ ለማስመለስ ታቅዶ ብር 582,950,708.43 (52%) በማስመለስ ማቀናነስ እንደተቻለ አብራርተዋል፡፡

➣ ከደን አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለዉጥ ስራዎች አኳያ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ለተሰማሩ ለ176 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ የተፅዕኖ ጥናት ሰነድ ገምግሞ ይሁንታ ፍቃድ ተሰጥቷል ፡፡

➣ በደን ልማት፣ ጥበቃና አጠቃቀም፣ በበጀት ዓመቱ በበልግና በመኸር በድምሩ 80.5 ሚሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል ፡፡

➣ የችግኞችን የመጽደቅ አቅማቸውን ለማሻሻል 131 ነባር ችግኝ ጣቢያዎችን ማጠናከር ተችሏል

6 አዲስ ሞዴል የችግኝ ጣቢያዎችን ማቋቋም መቻሉን ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸዉ አመልክተዋል።

በታጠቅ አበበ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *