ቢስት ባር ዕሴት የወል እውነትና የኅብረ ብሄራዊነት መሠረት ነው – የተከበሩ አቶ አገኘሁ ተሻገር




የቤንች ብሄር የዘመን መለወጫና የምስጋና በዓል የኾነው ቢስት ባር በሚዛን አማን ከተማ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢፌዲሪ ፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ የተከበሩ አቶ አገኘሁ ተሻገር፥ የቢስት ባር ዕሴት የወል እውነትና የኅብረ ብሄራዊነት መሠረት ነው ብለዋል።
ቢስት ባር ከተፈጥሮና ከግብርና ሥራዎች ጋር የሚገናኝ በመኾኑ ይህንን መልካም ዕሴት በማጠናከር የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
በዓሉ ኢትዮጵያዊያንን በአንድነት በማሰባሰብ የህዝቦች አንድነትን የሚያጠናክር፣ እርቅና ይቅርታ የሚደረግበት ታላቅ የማኅበረሰብ መገለጫ የኾነ በዓል እንደኾነም አቶ አገኘሁ ተናግረዋል።
የቢስት ባር ባህል ዕሴቱን ሳይለቅ ለትውልድ እንዲተላለፍ የታሪክ ምሁራን በቅንጅት እንዲሰሩም አቶ አገኘሁ አሳስበዋል።
በዕድገቱ በዛብህ
በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች መረጃዎችን ይከታተላሉን ![]()
በፌስቡክ https://www.facebook.com/sowestcommunication/
በድረገጽ www.southwestcomunications.gov.et
በኢንስታግራም https://instagram.com/southwest_communications
በትዊተር twitter.com/sweprs
በቲክቶክ https://www.tiktok.com/@southwest.communi
በቴሌግራም https://t.me/Debubmierab
በዩቲዩብ youtube.com/@southwestgovcommunication
በዋትስአፕ
https://whatsapp.com/channel/0029VbAiSCpGE56ue7VyJJ3x
በሊንክደን
https://www.linkedin.com/company/southwest-communications
በትሬድስ
https://www.threads.com/@southwest_communications
በብሉ ስካይ
