





ባለፉት ሥድስት ወራት 74 ሺህ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች በኢትዮጵያ የሚገኙ ብሔራዊ ፓርኮችን ጎብኝተዋል፡፡
ከእነዚህ ጎብኝዎችም በአጠቃላይ 62 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ለፋና ዲጂታል አስታውቋል፡፡
በአጠቃላይ ከተገኘው ገቢ 49 ነጥብ 8 ሚሊየን ያህሉ ከዱር እንስሳት ፍጆታዊ አጠቃቀም (ህጋዊ አደን) መሆኑንም አስረድቷል፡፡
ከኢ-ፍጆታዊ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ደግሞ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር መገኘቱን ነው ያስታወቀው፡፡
የተሻለ የጎብኝ ቁጥር ካስተናገዱት ብሔራዊ ፓርኮች መካከል÷ ነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ፣ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ ስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ፣ አብጃታ ሻላ ሐይቆች ብሔራዊ ፓርክ እና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተጠቅሷል፡፡
በኢትዮጵያ 27 ብሔራዊ ፓርኮች እንደሚገኙ ይወቃል ሲል ኤፍኤም ሲ ዘግቧል፡፡
