





የትምህርት ልማት ስራዎች
በትምህርት ለትውልድ ኢንሸቲቭ ከማህበረሰብ ተሳትፎ የትምህርት ቤቶች ደረጃ ለማሻሻል በተሰራው ስራ 711,748,341 ብር ማሰባሰብ ተችሏል።
በተሰበሰበው ሀብት 661 አዲስ መማሪያ ክፍሎች መገንባቱ፣ 1,417 ነባር መማሪያ ክፍሎችን የጥገና ስራ ተከናውኗል፡፡
በክልል ደረጃ በልዩ ንቅናቄ 36 ደረጃቸውን የጠበቀ ሞዴል ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ግንባታ የሚሆን 185,527,812 ብር በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
በአርብቶ አደር አካባቢ የትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል የቱልጊት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በክብርት ቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በኩል በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ግንባታው ተጠናቆና የውስጥ ቁሳቁስ ተሟልቶ በ2018 ትምህርት ዘመን ትምህርት ለማስጀመር ዝግጁ ተድርጓል፡፡
በቅድመ አንደኛ 101,300፣ በአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ-6ኛ) 476,589፣ (ከ7-8ኛ) 83,651 እና በሁለተኛ ደረጃ 87,332 በድምሩ ከቅድመ አንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል 748,872 የዕወቅዱ (79%) በመመዝገብ የመማር ማስተማር ሥራ ተከናውኗል፡፡
በ349 ትምህርት ቤቶች 44,312 ተማሪዎችን ምገባ ማድረግ ተችሏል፡፡
የትምህርት ግብዓት አቅርቦት እና ቴክኖሎጂ ስርፀትን ከማሻሻል አንጻር የተለያዩ መጽሐፍት በመሰራጨት ላይ መሆኑ፤
ጥምርታውን ለማሻሻል ተጨማሪ 885,000 መጽሐፍት ከቅድመ 1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል በመታተም ላይ ይገኛል፡፡
ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከ9-12ኛ ክፍል መጽሀፍት 1፡1 በሆነ ጥምርታ ለተማሪዎች ተደራሽ ተደርጓል።
የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን እጥረት ለመቅረፍ 608 አዲስ ዲፕሎማ እና 231 ሰርተፊኬት ዕጩ መምህራን ስልጠና መጀመራቸው፡፡
የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮች ብቃት እየመዘኑ የአቅም ማጎልበቻ አማራጮችን ለመዘርጋት በተያዘው ዕቅድ 11,612 እንዲመዘኑ ተደርጓል፡፡
በ2017 ዓ.ም በክልል ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ለ48,072 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ተሰጥቷል፡፡
38,688 ተማሪዎች የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ፈተና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡
በ2016 ዓ.ም በክልል ደረጃ ሀገራዊ ፈተና ከወሰዱ 16,872 መደበኛ ተማሪዎች መካከል በመደበኛና በሪሜዲያል 1,953 ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብቷል፣
በ2017 ዓ.ም በጠቅላላው 19,127 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡
የጤና ሥራዎችን በተመለከተ
የወባ ተዋሲያን በደማቸው የተገኘባቸው 1,207,730 አስፈላጊውን ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
ከፍተኛ የወባ ጫና ባለባቸው 42 ወረዳዎች 1,144,762 የአልጋ አጎበር ለማህበረሰቡ ቤት ለቤት ማሰራጨት ተችሏል፡፡
በእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎት 485,368 ሴቶች የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡
112,655 እናቶች የቅድመ ወሊድ አገልግሎት አንድ (1) የተከታተሉ ሲሆን አራት ጊዜና ከዚያ በላይ ለ 86,482 እናቶች አገልግሎቱን ለማከናወን ተችሏል፡፡
በሰለጠኑ የጤና ባለሙያዎች 64,435 እናቶች የወሊድ አገልግሎት አግኝተዋል፡፡
የደም ባንክ አገልግሎት 5952 ዩኒት ደም ለመሰብሰብ ታቅዶ 4732 (80%) ደርሷል፡፡
ከማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን አንጻር 421,541 አባላት ማፍራቱ መቻሉ፤ የአባላት ምጣኔ ሽፋን 75.6 % ደርሷል፡፡
ነባር አባላት እድሳትን 289,696 ለማደስ ታቅዶ 258,776 የማዐጤመ አባላትን በማደስ 89.3% ላይ ይገኛል፡፡
አዲስ አባላት 267,711 በአድስ አባል ለማድረግ ታቅዶ 162,765 (60.8%) ማፍራት ተችሏል፡፡
በማህበረሰብ ጤና መድን 445,736,763 ብር በመሰብሰብ ባንክ ገብቷል፡፡ ባንክ ከገባዉ ገንዘብ 139,544,607 ብር ወደ ጤና ተቋም ተላልፎ የመድሐኒት ግዥ የተፈፅሟል።
12 የማህበረሰብ መድኃኒት ቤት አገልግሎት በተለያዩ ከተሞች ተከፍቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛሉ።
ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ
153 የቱሪዝም ሃብቶች ልየታና ትንተና ስራ ተከናውኗል፣
የቱሪስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን ብቃታቸው በማረጋገጥ እውቅና መስጠት 120 ተከናውኗል ፡፡
በስፖርት ዘርፍ ከመንግስት፣ ከህብረተሰብና ከተለያዩ ምንጮች 55,281,189 መሰብሰብ ተችሏል።
በሚዛን አማን ስፖርት አካዳሚ 27 ሰልጣኞችን በአትሌቲክስ ስፖርት እየሰለጠኑ ይገኛሉ።
በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ
ከከሴቶች መብትና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት አኳያ ከሴት ልጅ ግርዛትና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች 62 ቀበሌዎችን ነፃ ማድረግ ተችሏል፡፡
93647 ሴቶችን በቁጠባ እንዲሳተፉ ተደርጓል ፡፡
በክልሉ 82,940 ሴቶች የገጠር መሬት ባለቤትነት ተረጋግጦላቸዋል ፡፡
658,315 ወጣቶች በተለያዩ ከክረምት እስከ በጋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሳተፉ ተድርጓል፡፡
ይህም አገልግሎት በገንዘብ ሲተመን ብር 618,020,980 የሚገመት ነው፡፡
658,315 ወጣቶች በተለያዩ ከክረምት እስከ በጋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሳተፉ ተድርጓል፡፡
ይህም አገልግሎት በገንዘብ ሲተመን ብር 618,020,980 የሚገመት ነው፡፡
በጌታሁን ግርማ
