


የክልሉን ሠላም ለማጽናት 491,389 የህብረተሰብ ክፍሎችን በሰላም፣ በብዝሃነት፣ በአብሮነትና በሰላም ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤ በመፍጠር ተችሏል ፣
60 የሰላም ምክር ቤቶችን በማጠናከር ወደ ስራ ለማስገባት ተችሏል።
የሃይማኖት ተቋማት ለሁለንተናዊ ሠላም ግንባታ ያላቸው ሚና ለማሳደግ
32 የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ አደረጃጀቶችን ለማጠናከርና መደገፍ ስራ ተሰርቷል ፣
በየደረጃው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ከቀረቡ 63 የሃይማኖት ነክ መልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ተችሏል፡፡
ከአጎራባች ክልሎች በሚያዋስኑ ዞኖች የሚሰተዋሉ የጸጥታ ሥጋቶችን ለመቀነስና ሠላሙን ለማጽናት 28 ዙር ዙር ምክክር ተደርጓል።
39 ከፍተኛ ስጋት ያለባቸውን ቀበሌያትን ወደ አንጻራዊ ሠላም እና 187 መለስተኛ ስጋት የሚስተዋልባቸውን ቀበሌያትን ወደ አስተማማኝ ሠላም ማሸጋገር ተችሏል፡፡
የወሳኝ ኩነቶች የምዝገባ ሽፋንን በክልሉ ከሚገኙ 930 የምዝገባ ኮድ ከተሰጣቸው ቀበሌያት መካከል 90% (837 ቀበሌ) ለማድረስ ታቅዶ 837 (100%) ማከናወን ተችሏል፡፡
የሚሊሻ አቅም በማጠናከረ በሚልሻ ኃይል በህግ የሚፈለጉ 5,549 ተጠርጣሪዎችን ለህግ እንዲቀርቡ ተደርጓል፡፡
የወንጀል መከላከል ሥራውን ውጤታማነት ለማረጋገጥ 3,799 የፖሊስ አመራርና አባላትን መገምገምና ማጥራት ተችሏል፡፡
ከግምገማው በመነሳት 55 አመራሮች ከቦታቸው እንዲነሱ፣ 739 አመራርና አባላት በማስጠንቀቂያ፣44 በዲሲፒሊን እንዲጠየቁ፣ 34 አመራርና አባላት ለህግ እንዲቀርቡ ተደርጓል፡፡
የፍትህ ስራዎች አፈጻጸም
በሁሉም የወንጀል አይነቶች ለዐቃቤ ህግ 9,195 ቀርቦ አስተያየት እና ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የምርመራ መዝገቦችን የማጥራት ምጣኔ 93.2% ተከናውኗል፡፡
7,151 የወንጀል ክስ መዝገቦች ላይ በፍርድ ቤት ክርክር በማሄድ በፍርድ ቤት ውሳኔ ሰጥቶበታል፡፡
5,806 መዝገቦች በተከሳሾች ላይ የጥፋኝነት እና የቅጣት ዉሳኔ፤ 292 መዝገቦች ላይ ተከሳሾች በነጻ እንዲሰናበቱ፣ 1,763 መዝገቦች ለሚቀጥለዉ የዞሩ ናቸዉ፡፡
በሙስና ወንጀል ጉዳዮች ለዐቃቤ ህግ 197 መዝገቦች ቀርቦ 189 መዝገቦች ላይ የተለያዩ ህጋዊ አስተያትና ዉሳኔ መስጠት የተቻለ ሲሆን የማጥራት ምጣኔን 95.9% ተከናውኗል፡፡
በታክስና ኢኮኖሚ ነክ ወንጀል 137 መዝገቦች ላይ ህጋዊ አስተያትና ዉሳኔ የተሰጠ ሲሆን የማጥራት ምጣኔ 97.5% ለማድረስ ታቅዶ 95.8% ማድረስ ተችሏል፡፡
በሴቶችና ህፃናት የሚፈጸሙ ልዩ ልዩ ወንጀሎች 498 መዝገቦች ምርመራቸዉ ተጠናቆ ለዐቃቤ ህግ የደረሱ ሲሆን በ488 መዝገቦች ላይ ዉሳኔ ተሰጥቷል፡፡
6,470 በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወደ ማረሚያ ቤት የተላኩ የቀጠሮ እስረኞችና የሕግ ታራሚዎችን በመቀበል እያስተናገደ ይገኛል፡፡
በመታረም ላይ ለሚገኙ 1,327 ታራሚዎች ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የቀለም ትምህርት እንዲያገኙ ተድርጓል፡፡
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት ስራዎች አፈጻጸም
የጸረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ትግል ዕቅድና አፈጻጸም ከመጠን፣ ከጥራት እና ከጊዜ አንጻር በመገምገም 2 ዙር ግብረ-መልስ ተሰጥቷል፡፡
ብልሹ አሰራር ዉስጥ የተሳተፉ የመንግሥት ሠራተኞች 238 ሲሆኑ አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፣
ህጋዊ እርምጃ የተወሰደባቸዉ 6 ናቸዉ፡፡
በመልካም አስተዳደር ጉድለት 540 አቤቱታ ቀርቦ 534 (98%) ምላሽ እንዲያገኝ ተድርጓል፡፡
235 ባለሙያዎችን በ 2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ እንዲከታተሉ በመመልመል ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንዲገቡ ማድረግ ተችሏል፡፡
በ43 ተቋማት የሰው ኃይል ስምርት 11,185 ተፈትሾ 1,462 ጉድለት የተገኘ ሲሆን ብር 6,094,633 ከብክነት ማዳን ተችሏል፡፡
23,392 የትምህርት ማስረጃ እስካን በማስደረግ ለማሰባሰብ ታቅዶ ለመፈጸም ተችሏል፣
የአስተዳደር ፍ/ቤት አፈጻጸም፡- አዲስ የይግባኝ መዝገቦች 141፣ ከባለፈው በጀት ዓመት 02 የተላለፈ በድምሩ 143 መዝገብ ቀርቦ 140 መዝገቦች ላይ ውሳኔ በመስጠት 3 መዝገቦች ወደ ቀጣዩ በጀት ዓመት በቀጠሮ ተላልፏል፡፡
የመንግስት የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሥራዎች አፈጻጸም
10 ሁነቶችንና መድረኮችን ለማሰተባበርና ለመምራት ታቅዶ 11፣
የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉን ተወዳዳሪነትንና ውጤታማነትን ለማሳደግ የሕግ ማዕቀፍ 2 የስራ ማኑዋልና መመሪያ ተዘጋጅተዋል፣
ቅንጅታዊ አሠራሮችን በመዘርጋት የዲጂታል ሚዲያ ለማሳደግ ለሚዲያ በቋሚነት 24 ሀገራዊና ክልላዊ ወቅታዊ አጀንዳዎችን መስጠት መቻሉ፣
በሚዲያ ሥራዎች የህዝብ አስተያየት ዳሰሳ እና የአዝማሚያ ትንተና ለማድረግ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ሚዲያዎችን ለመለየት 5 ታቅዶ 5 ተከናወኗል።
በሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ 20 ጊዜ ጋዜጣዊ መግለጫ መሰጠቱ እና 20 ጊዜ ፕሬስ ሪሊዞችን ተሰጥቷል ፣
የስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ስራዎች አፈጻጸም
ቀልጣፋና ግልፅነት ያለው የአስቸኳይ ሙስናን ከመከላከል ረገድ 729 ጥቆማዎች በፅሁፍ፣ በስልክ፣ በአካል እና የተለያዩ መወበሎ መቻሉ፣
ከነዚህ አስቸኳይ መከላከል ስራ የተሰራ 292፣ ለፍትህ አካላት ተላልፎ የተሰጠ 124፣ ምክር አገልግሎት ያገኘ 16፣ ህግ ከለላ እንድሰጥ የተደረገ 11፣
ተመዝብሮ የነበረ እና በኦዲት ግኝት ክትትል ተደርጎ ብር 45,618,878.2 ማስመለስ ተችሏል፡፡
በአጠቃላይ በአስቸኳይ መከላከል እና በኦዲት ብር 224,490,270.7 ከምዝበራ ማዳን ተችሏል፡፡
