የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው?

Spread the love

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-

👉የአፈር ማዳበሪያ ስርጭት ላይ መዘግየት እንዳይፈጠር ምን እየተሠራ ነው?

👉 ወደ ታላቁ ህዳሴ ግድብ የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጧል፤ ይህን ለማስቀጠል ምን እየተሠራ ነው?

👉 የስራ እድል ፈጠራ ለሴቶች እና ለክልሎች ያለው አካታችነት ቢብራራልን፤

👉 ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር እና ሰላም የማስከበር እርምጃን ለማጣጣም ምን እየተሠራ ነው?

👉 በቤንሻንጉል ለኑሮ ውድነት ማካካሻ ጭማሪ ቢደረግም፤ የመምህራን ያልተከፈለ ውዝፍ ደሞዝ መኖሩ እንዴት ይታያል?

👉 በመተከል ስር የሰደደው የኮንትሮባድ አሰራር እንዲፈታ ምን ታስቧል?

👉 ተጀምረው የተጓተቱ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ለማፋጠን ምን ዕቅድ ተይዟል?

👉 ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልተመለሱ ተማሪዎች መኖራቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፤ ይህን ለመፍታት ምን እየተሠራ ነው?

👉 ወረርሽኞችን ቀድሞ ከመከላከል የተወሰዱ እርምጃዎች ምንድን ናቸው? የመድኃኒት አቅርቦትን ለማሻሻልስ ምን እየተሠራ ይገኛል?

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *