የክልሉ የድጋፍና ክትትል ቡድን በካፋ ዞን ወቅታዊ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎችን ስያካሂድ የነበረውን አፈጻጸም እየገመገመ ይገኛል።

Spread the love

ግምገማው በዋናነት በመደበኛ በፓርቲ ስራዎችና በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ የተቀመጡ ሀገራዊ 6ቱ የትኩረት አቅጣጫ ግቦችን ስኬታማ ለማድረግ በዞኑ እየተሰራ ያለው አፈጻጸም በጥንካሬና በጉድለት በመገምገም ተግባራቶች በተቀመጠላቸው ጊዜ ሰሌዳ ስኬታማ ለማድረግ ታሳብ ያደረገ ነው።

ለግምገማ መድረኩ የተዘጋጀውን የዞኑን ወቅታዊ አፈጻጸም ሪፖርት የካፋ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ታከለ ታምሩ እያቀረቡ ይገኛል ።

በመድረኩ ላይ የክልሉ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ገነት መኩሪያ ፣ የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ የሽዋስ ዓለሙ፣ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽን ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ዳንኤል ያዙ እና የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ሀላፊ አቶ ተስፋዬ መኩሪያን ጨምሮ የካፋ ዞን አስተባባሪ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *