




በምዕራብ ኦሞ ዞን ከቃል እስከ ባህል የዞን የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራሮች የዉይይት መድረክ በጀሙ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በሀገራችን የተጀመረው ሥራዎች የአረንጓዴ አሻራ አረጋዊያን የመደገፍ የልማት ሥራዎች ከወቅታዊነት በሻገር ባህል እንዲሆኑ ማድረግ ይጠበቃል ተብሏል።
ቃሎቻችን ወደ ባህል በመቀየር ጠንካራ እና በኢኮኖሚ ተወዳዳሪ የሆነ ሀገር መፈጠር እንደሚገባ ተገልጿል።
ህልማችን ደግሞ የበለፀገች ኢትዮጵያ ማየት ከመሆኑም ጋር ተይዘው ሥራዎቻችን በትኩረት መስራት ይጠበቃል ተብሏል።
በመድረኩ የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮምቴ አባልና የክልሉ የህብረት ሥራ ኤጀንሲ አቶ ቀበሌ መንገሻ ፤የክልሉ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሃላፊ አቶ ተመሰገን ከበደ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸዉ ኬኒ እና ከፍተኛ የዞን አመራሮች ጨምሮ ተገኝተዋል።
ከቃል እስከ ባህል የዉይይት መድረክ ላይ የዞኑ አጠቃላይ አመራሮች የወረዳ እና የከተማ አስተዳደር አጠቃላይ አመራሮች ተገኝተዋል።
ዘገባዉ የምዕራብ ኦሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ
