በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በ 1 ሺህ 85 ጣቢያዎች እየተሰጠ እንደሚገኝ ተገለጸ

Spread the love

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አልማው ዘውዴ ከዛሬ ጀምሮ የሚሰጠውን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዳዉሮ ዞን ታርጫ ከተማ አስተዳደር አዲስ ፋና ትምህርት ቤት ተገኝተው አስጀምረዋል።

በክልሉ ከ1ሺህ 86 በላይ የማስተፈኛ ጣቢያዎች መካከል ከ38 ሺህ 5 መቶ 93 በላይ ተማሪዎች በሰባት የትምህርት ዓይነቶች ፈተናውን እየተፈተኑ ይገኛሉ።

በቀጣይም ከ48 ሺህ በላይ የ6 ክፍል ተማሪዎች በ5 የትምህርት ዓይነቶች እንደሚፈተኑም አቶ አልማዉ ገልጸዋል።

ፈተናዉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች እየተሰጠ ይገኛል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *