ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብሄራዊ ፈተና በሚዛን-ቴፒና ቦንጋ የዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝደንቶች፣ ምክትል ፕሬዚደንቶች እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸዉ አካላት በተገኙበት ተጀምሯል።

Spread the love

የሁለተኛው ዙር የማኅበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተፈታኞች ፈተናቸውን በእንግሊዝኛ ትምህርት ዓይነት መጀመራቸውን ከዩኒቨርሲቲዎቹ መረጃ መወቅ ተችሏል።

የሁለቱም ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንቶች ባስተላለፉት መልዕክት ለተማሪዎች መልካም ምኞታቸውን ገልጸው ፈተናውን ተረጋግተው መስራት እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።

ፈተናው ከዛሬ ጀምረው ሶስት ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በዚህኛውም ዙር የፈተና አሰጣጡ በወረቀት እና በበይነ-መረብ /Online/ እንደሚሰጥ ታውቋል።

በአሻግሬ ገ/ወልድ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *